የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በአማራ ክልል በ42 የተለያዩ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራ ተከናውኗል

Jul 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ) ፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ42 የተለያዩ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራ መከናወኑን የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ አማካሪ ሽቤ ክንዴ፤ በተለይም በከተሞች ልማት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተከናወኑ አበይት ተግባራትን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም በክልሉ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራዎችን በማስፋፋት ዘመናዊ በማድረግ ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንትና ለጉብኝት ጭምር ምቹ ማድረግ ስለመቻሉ አንስተዋል።

በክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ42 የተለያዩ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራ ስለመከናወኑ ጠቅሰው በዚህም የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

የኮሪደር ልማቱ የእግረኛ፣ የተሽከርካሪ፣ የብስክሌት መንገድን ጨምሮ የአረንጓዴ ልማት፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ የመዝናኛ ስፍራዎችና መሰል አገልግሎቶችን አካቶ የተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በተያዘው በጀት ዓመትም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።

በልማቱ ከ214 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ስራ እንዲሁም ከ100 ሄክታር በላይ የተለያዩ አካባቢዎችን በአረንጓዴ ልማት የማስዋብ ስራ ተሰርቷል ብለዋል።

በዚህ የልማት ስራ ከ199 ሺህ 700 ለሚበልጡ ወገኖች የስራ እድል ስለመፈጠሩ አንስተው ልማቱ ቀጣይነት ይኖረዋል ብለዋል።

የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት የልማት እንቅስቃሴም በ205 ከተሞችና ክፍለ ከተሞች 281 ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ሲሆን አብዛኞቹ ተጠናቀው ለህዝብ አገልግሎት እንዲውሉ መደረጉንም አንስተዋል።

በቀጣይም ልማቱን ወደ ሌሎች ከተሞች ለማስፋት መታቀዱን ያነሱት አቶ ሽቤ፤ የዜጎች እገዛና ተሳትፎ ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026