የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተካሄዱ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ ሆነናል

Jul 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ከሚሴ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፡-ባለፉት የለውጥ ዓመታት ተግባራዊ በተደረጉ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በከሚሴ ከተማ "የኢትዮጵያ ከተሞች የኮሪደር ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው ስለ ኢትዮጵያ የተሰኘ የምክክር መድረክ ተካሂዷል።


በምክክር መድረኩ ላይ የተገኙት የከሚሴ ከተማ ነዋሪ ሼህ የሱፍ ይማም እንደገለፁት፣ በለውጡ ዓመታት በተቀናጀ መንገድ ሰላምን ከማስፈን ባሻገር ተግባራዊ በተደረጉ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ ሆነናል።

ከለውጡ በፊት ከተማዋ በልማት ወደ ኋላ የቀረች ከመሆኑ በተጨማሪ ግጭቶች የሚታዩባት እንደነበር አስታውሰዋል።

አሁን ላይ የተሟላ ሰላም ከመሰፈኑ ባሻገር በከተማዋ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶችመሟላታቸው ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።


ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ የባቲ ከተማ ነዋሪ አቶ ኡመር መሐመድ በበኩላቸው፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሚሰሩ የልማት ስራዎች ማሕበረሰቡ ለረዥም ጊዜ ሲያነሳቸው ለነበሩ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ናቸው።

በተለይም የአካባቢውን ሰላም ከማጽናት ባለፈ የዲጂታል አገልግሎት በተሻለ ጥራት ተደራሽ በማድረግ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።

የአካባቢያችን ሰላም ተጠብቆ በተሰሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ ሆነናል ያሉት ደግሞ የጨፋ ሮቢት ከተማ ነዋሪ አቶ አሊ ሰይድ ናቸው።


ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከአጎራባች ዞኖችና ክልሎች ጋር ያለንን ግንኙነት በማጠናከር በልማት ጭምር መተሳሰሩ ይበልጥ እንድንቀራረብና በጋራ ተጠቃሚ መሆን እንድችል አድርጓል ነው ያሉት።

የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በበኩላቸው፣ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ህብረተሰቡን በማሳተፍ ሰላምን ለማስፈን በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል ነው ያሉት ።

ከሰላም ማስክበር ስራው በተጓዳኝ የህዝቡን የልማት ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎችን በማከናወን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደተቻለ ገልፀዋል።


በመድረኩ የከተማና መሰረት ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒን ጨምሮ የፌዴራል ፣ የክልል ፣ የዞንና የከተማ አመራሮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026

በድሬደዋ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰዱ

ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...

Jul 21, 2026

መንግሥት የሎጂስቲክስ ዘርፉን በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...

Jul 15, 2026

ሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስ...

Jul 6, 2026