🔇Unmute
ከሚሴ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፡-ባለፉት የለውጥ ዓመታት ተግባራዊ በተደረጉ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በከሚሴ ከተማ "የኢትዮጵያ ከተሞች የኮሪደር ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው ስለ ኢትዮጵያ የተሰኘ የምክክር መድረክ ተካሂዷል።

በምክክር መድረኩ ላይ የተገኙት የከሚሴ ከተማ ነዋሪ ሼህ የሱፍ ይማም እንደገለፁት፣ በለውጡ ዓመታት በተቀናጀ መንገድ ሰላምን ከማስፈን ባሻገር ተግባራዊ በተደረጉ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ ሆነናል።
ከለውጡ በፊት ከተማዋ በልማት ወደ ኋላ የቀረች ከመሆኑ በተጨማሪ ግጭቶች የሚታዩባት እንደነበር አስታውሰዋል።
አሁን ላይ የተሟላ ሰላም ከመሰፈኑ ባሻገር በከተማዋ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶችመሟላታቸው ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።

ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ የባቲ ከተማ ነዋሪ አቶ ኡመር መሐመድ በበኩላቸው፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሚሰሩ የልማት ስራዎች ማሕበረሰቡ ለረዥም ጊዜ ሲያነሳቸው ለነበሩ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ናቸው።
በተለይም የአካባቢውን ሰላም ከማጽናት ባለፈ የዲጂታል አገልግሎት በተሻለ ጥራት ተደራሽ በማድረግ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።
የአካባቢያችን ሰላም ተጠብቆ በተሰሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ ሆነናል ያሉት ደግሞ የጨፋ ሮቢት ከተማ ነዋሪ አቶ አሊ ሰይድ ናቸው።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከአጎራባች ዞኖችና ክልሎች ጋር ያለንን ግንኙነት በማጠናከር በልማት ጭምር መተሳሰሩ ይበልጥ እንድንቀራረብና በጋራ ተጠቃሚ መሆን እንድችል አድርጓል ነው ያሉት።
የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በበኩላቸው፣ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ህብረተሰቡን በማሳተፍ ሰላምን ለማስፈን በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል ነው ያሉት ።
ከሰላም ማስክበር ስራው በተጓዳኝ የህዝቡን የልማት ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎችን በማከናወን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደተቻለ ገልፀዋል።

በመድረኩ የከተማና መሰረት ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒን ጨምሮ የፌዴራል ፣ የክልል ፣ የዞንና የከተማ አመራሮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026