የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ከ55 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል

Jul 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር ፤ሐምሌ 15/2018( ኢዜአ)፡-በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ55 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን የከተማ አስተዳደሩ ስራና ክህሎት መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ዘመነ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው በጀት አመት ለ45 ሺህ 300 ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር ታቅዶ ከአቅድ በላይ ከ55 ሺህ የሚሆኑ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።

የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች ውሰጥም ከ38 ሺህ በላይ ለሚሆኑት ቋሚ፣ቀሪዎቹ ደግሞ ጊዜያዊ የስራ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

የስራ እድሉ በውጭ ሀገር የስራ ስምሪት፣ በከተማ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ ፣ ኮንስትራክሽን፣ በአገልግሎትና ሌሎች ዘርፎች የተፈጠረ መሆኑን ተናገረዋል።

በዚህ ወቅት ሦስት ሺህ 65 የሚደርሱ ኢንተርፕራይዞችን በማደራጀት ወደ ስራ ማስገባት የተቻለ መሆኑንም ነው ያስረዱት።

ለስራ እድል ተጠቃሚዎች ከ321 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆን መደበኛና ተዘዋዋሪ ብድር ማመቻቸት እንደተቻለም ነው የጠቀሱት።

በተጨማሪም በ128 ሚሊዮን ብር ወጭ የስራ እድሉ ለተፈጠረላቸው ዜጎች የመስሪያ ማሽኖችን ማቅረብ መቻሉን ጠቁመው 125 ሼዶችና ኮንቴነሮችንም ማስተላለፍ መቻሉን አስገንዝበዋል።

የስራ እድል ከተፈጠረላቸው መካከል ወይዘሮ እናንዬ ታምሩ እንደገለጹት፤ ከ40 በላይ ሴቶች በአንድ ላይ ተደራጅተን አሳ የማቅረብ ፣የማዘጋጀትና የማከፋፈል ስራ በመስራት ውጤታማ ሆነናል።

የማህበሩ አባላትም ከሚያገኙት ገቢ ከእለት ፍጆታ ባለፈ የቁጠባ ባሕላቸውን ለማዳበር ያስቻላቸው በመሆኑም በዘርፉ በስፋት ወደ ስራ ለመግባት ጥረት እያደረጉ መሆኑን ነው የገለጹት።

ሁለት ሆነው በመደራጀት በጀመሩት የልብስ ስፌት ስራ ውጤታማ በመሆኑ ተጨማሪ ማሽኖችን በመግዛት ለሌሎች ስራ ለመፍጠር ጥረት እያደረጉ መሆኑን የተናገረችው ደግሞ ወጣት እናኑ ደሴ ናት።

አሁን ላይ በገቢም ሆነ በማምረት የተሻለ ቁመና ላይ እንገኛለን፤ለዚህም በከተማ አስተዳደሩ የተደረገልን ብድርና ሌሎች ድጋፎች ትልቁን ድርሻ ይወስዳል ብላለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ የመኸር አዝመራን ውጤታማ  ለማድረግ ለኩታ ገጠም እርሻና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቷል

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...

Jul 23, 2026

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026

በድሬደዋ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰዱ

ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...

Jul 21, 2026

መንግሥት የሎጂስቲክስ ዘርፉን በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...

Jul 15, 2026