🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራዎችን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል ሙፈሪያት ካሚል ገለፁ።
የብልፅግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።

የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባልና የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል በመድረክ ላይ እንደገለጹት፤ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራዎችን በማጠናከር የዜጎች ተጠቃሚነትን ከማረጋገጥ አኳያ ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል።
በበጀት ዓመቱ የሀገር ውስጥ የሥራ ዕድል፣ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት እና የቴክኖሎጂ አማራጮችን በመጠቀም የርቀት ሥራ በትኩረት መሰራቱን አንስተዋል።
በዚህም መሠረት በሶስቱ ዋና ዋና አማራጮች ለአምስት ነጥብ አራት ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ከአምስት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን በላይ ማከናወን መቻሉን አብራርተዋል።
ለዜጎች የተፈጠሩት የስራ እድሎች በግብርና፣ በአገልግሎት፣ በኢንዱስትሪ፣ በውጭ አገር የስራ ስምሪት እና በርቀት የተፈጠሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ይህ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ የፓርቲው ቅርብ አቅጣጫና ድጋፍ እንዲሁም የባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመዋል፡፡
በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ከ 631 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ስምሪት በማመቻቸት ዜጎች ተጠቃሚ መሆናቸውን አመልክተዋል።
ከተለያዩ የአረብ ሀገራት በተጨማሪ ወደ ስድስት የአውሮፓ ሀገራትም ዜጎችን መላክ መጀመሩን ጠቅሰዋል፡፡

ሀገራት እያሳዩ ባሉት ፍላጎት መሠረት ስምምነቶች ተፈራርመው ዜጎች አስፈላጊውን የሙያና የቋንቋ ስልጠና አግኝተው ወደ ሥራ እንዲሰማሩ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
የዲጂታል እና የርቀት ሥራ (Remote Work) የዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም በርቀት ሥራ ከ41ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉንም አብራርተዋል፡፡
ለዚህም የአምስት ሚሊዮን ኢትዮ-ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ጋር የተደረገ ማስተሳሰር ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቅሰዋል፡፡
በተጨማሪም ወደ 70 የሚጠጉ የቴክኒክና ሙያ ማዕከላት የዲጂታላይዜሽን ፕሮግራም እንዲቀርፁ ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026