የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በጅማ ዞን ከ1 ሺህ 600 በላይ አርሶ አደሮች ወደ ኢንቨስትመንት ተሸጋግረዋል

Jul 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦ በ2018 በጀት ዓመት በጅማ ዞን ከ1 ሺህ 600 በላይ አርሶ አደሮች ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን የዞኑ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ወይዘሮ ዘሊካ ቡላ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በዞኑ ለኢንቨስትመንት ያለውን አቅም ወደ ልማት ለመቀየር የአሠራርና የሕግ ማዕቀፎች ተዘርግተዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ በግብርና፣ አነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞችና በኅብረት ሥራ ማኅበራት ተሰማርተው የነበሩ 1 ሺህ 739 አልሚዎች ሀብት አፍርተው ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን ገልጸዋል።

ባለሀብቶቹ ወደ ኢንቨስትመንት የተሸጋገሩት 5 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ መሆኑን ጠቁመዋል።

አልሚዎቹ በተሰማሩበት ዘርፍ ውጤታማ ሆነው ወደ ኢንቨስትመንት እንዲሸጋገሩ በመንግሥት 8 ሺህ 27 ሄክታር መሬት የቀረበ ሲሆን፣ 120 ሚሊዮን ብር ብድር መሰጠቱን ገልጸዋል።

ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገቡም ከ22 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ይፈጥራሉ ብለዋል።

በዞኑ 2 ሺህ 495 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በሥራ ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው እነዚህ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ከ55 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በቋሚነትና በጊዜያዊነት የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል።

በዞኑ በዴዶ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ጃፈር አብዱልቃድር፤ በ2012 ዓ.ም ተደራጅተው በ50 ሺህ ብር መነሻ ካፒታል በግብርና ሥራ ላይ ተሰማርተው እየሠሩ እንደነበር ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት ካፒታላቸውን በማሳደግና ትርፋማ በመሆን ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን ገልጸዋል።

ማኅበራቸው ከ60 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰው፣ በቀጣይም ሥራውን በማስፋት በርካታ ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ አቅደው እየሠሩ እንደሚገኙ አንሥተዋል።

ወጣት ሚሊዮን ዳመነ በበኩሉ፤ በመንግሥት በተመቻቸላቸው የብድር አገልግሎት በሕንፃ ግንባታ ዘርፍ በማኅበር ተደራጅተው በመሥራት ካፒታላቸውን በማሳደግ ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገር መቻላቸውን ተናግሯል።

በኢንቨስትመንት ለመሰማራት ዞኑ ምቹ እና በርካታ አማራጮች ያለው ከመሆኑም ባሻገር መንግሥት የሚያደርግላቸው ድጋፍ እና ክትትል የበለጠ ለመሥራት ተነሣሽነትን እንደፈጠረላቸው አስታውቋል።

በዞኑ በቀጣይ የኢንቨስትመንት ቅበላ አቅምን ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑም ተጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026