የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በአሪ ዞን የመኸር አዝመራን ስኬታማ ለማድረግ የግብአት አቅርቦትና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ እየተሰራ ነው

Jul 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦ በአሪ ዞን የመኸር አዝመራን ስኬታማ ለማድረግ የግብአት አቅርቦትና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ ።

በዞኑ የ2018/19 የመኸር አዝመራ የማስጀመሪያ መርሃ- ግብር እየተካሄደ ነው።


የአሪ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ገረመው ኃይለማርያም በዚሁ ወቅት እንዳሉት የግብርና ዘርፉን በማዘመን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የስራ እድል ፈጠራን ለማስፋት እየተሰራ ነው ።

በዞኑ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻለ የግብአት አቅርቦት እንዲኖር ከማድረግ ባለፈ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማጎልበት ሞዴል አርሶ አደሮችን ለማፍራት እየተቻለ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይ በበጋው ወራት የተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የመኸር አዝመራውን ውጤታማ ለማድረግ መደላድል ፈጥረዋል ነው ያሉት።

የአሪ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ጉራልቅ ይዥማልቅ በበኩላቸው፤ በዞኑ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅእኖን የሚቋቋም ግብርናን እውን በማድረግ ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።


ለዚህም የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃን ጨምሮ የአረንጓዴ ልማት ስራዎች በተለየ ትኩረት እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ግብርናን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ በመስኖ ልማት ላይ ትኩረት ለማድረግም የገፀ ምድርና የከርሰ ምድር የውሃ አማራጮች ጥቅም ላይ መዋላቸውን አስረድተዋል።

የመኸር አዝመራውን በታቀደው ልክ ስኬታማ ለማድረግም አርሶ አደሮች የግብርና ባለሙያዎችን ምክር በመቀበል፣ የተሻሻሉ ዝርያና ቴክኖሎጂዎችን እንዲጠቀሙ እየተደረገ ነው ብለዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ከጂንካ ዩኒቨርስቲ ፣ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ፣ከጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከል እና የአጋር ድርጅት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026