የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የባሕርዳር ከተማን የተሞክሮ ማዕከል ለማድረግ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እየተደረገ ነው

Jul 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡-የባህር ዳር ከተማ የልማትና እድገት የተሞክሮ ማዕከል ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሞላ መልካሙ(ዶ/ር) ገለጹ።

የባህርዳር ከተማ አስተዳደር የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት አፈጻጸምን የሚገመግምና የአዲሱ በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ መድረክ ዛሬ አካሂዷል።


የቢሮ ኃላፊው ሞላ መልካሙ(ዶ/ር) እንደገለጹት በክልሉ የሚገኙ በርካታ ከተሞችን ለንግድ፣ ቱሪዝምና ለኑሮ የተመቹ ለማድረግ ሁለገብ የልማት ስራ እየተከናወነ ይገኛል።

የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በማከናወን ውብ፣ ሳቢና ማራኪ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የባህር ዳር ከተማ በሰፋፊ የአስፋልት መንገዶች፣ በኮሪደር ልማት፣ በስማርት ሲቲ ትግበራ፣ የአረንጓዴ ልማትና ሌሎች የልማት ስራዎች ካሳየችው እድገት በመነሳት የተሞክሮ ማእከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

እየተካሄደ የሚገኘው ሁሉን አቀፍ ልማት ከተማዋን ለኢንዱስትሪ፣ ኮንፈረንስ ቱሪዝም፣ ንግድና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ምቹ ሁኔታ የፈጠረ መሆኑን አብራርተዋል።

ቢሮው በከተማዋ የሚካሄዱ የልማት ስራዎች በጥራትና በፍጥነት እንዲከናወኑ እያደረገ ያለውን ክትትልና ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።


የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ አስሜ ብርሌ በበኩላቸው፤ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ የልማት ስራዎች ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ የሰጡ ናቸው ብለዋል።

የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል በቀጣይ የዲጂታል መሠረተ ልማትን የበለጠ በማስፋፋት የአገልግሎት አሰጣጥ ችግርን ለመቅረፍ በተሻለ መንገድ እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።

በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ ስኬቶች የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ሥራ ውጤት ናቸው ያሉት ደግሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ስራ አስኪያጅ አቶ ተሻገር አዳሙ ናቸው።

በመጀመሪያውና 2ኛው ዙር ብቻ ስምንት ነጥብ ስድስት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ማጠናቀቅ መቻሉን ጠቁመው 3ኛው ዙርም በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።

የተቀናጀ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በማፋጠን የባሕርዳር ከተማን ሁለንተናዊ ተመራጭነት በተጨባጭ የማረጋገጥ ጉዳይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል።

በ2019 በጀት ዓመት የታቀዱ የልማት ሥራዎችን በጥራትና በፍጥነት በማከናወን የከተማዋን ህዝብ ተጠቃሚ ለማደረግ በቅንጅት እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።

በመድረኩ የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላተ ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026