የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የባሕርዳር ከተማን የተሞክሮ ማዕከል ለማድረግ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እየተደረገ ነው

Jul 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡-የባህር ዳር ከተማ የልማትና እድገት የተሞክሮ ማዕከል ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሞላ መልካሙ(ዶ/ር) ገለጹ።

የባህርዳር ከተማ አስተዳደር የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት አፈጻጸምን የሚገመግምና የአዲሱ በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ መድረክ ዛሬ አካሂዷል።


የቢሮ ኃላፊው ሞላ መልካሙ(ዶ/ር) እንደገለጹት በክልሉ የሚገኙ በርካታ ከተሞችን ለንግድ፣ ቱሪዝምና ለኑሮ የተመቹ ለማድረግ ሁለገብ የልማት ስራ እየተከናወነ ይገኛል።

የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በማከናወን ውብ፣ ሳቢና ማራኪ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የባህር ዳር ከተማ በሰፋፊ የአስፋልት መንገዶች፣ በኮሪደር ልማት፣ በስማርት ሲቲ ትግበራ፣ የአረንጓዴ ልማትና ሌሎች የልማት ስራዎች ካሳየችው እድገት በመነሳት የተሞክሮ ማእከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

እየተካሄደ የሚገኘው ሁሉን አቀፍ ልማት ከተማዋን ለኢንዱስትሪ፣ ኮንፈረንስ ቱሪዝም፣ ንግድና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ምቹ ሁኔታ የፈጠረ መሆኑን አብራርተዋል።

ቢሮው በከተማዋ የሚካሄዱ የልማት ስራዎች በጥራትና በፍጥነት እንዲከናወኑ እያደረገ ያለውን ክትትልና ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።


የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ አስሜ ብርሌ በበኩላቸው፤ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ የልማት ስራዎች ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ የሰጡ ናቸው ብለዋል።

የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል በቀጣይ የዲጂታል መሠረተ ልማትን የበለጠ በማስፋፋት የአገልግሎት አሰጣጥ ችግርን ለመቅረፍ በተሻለ መንገድ እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።

በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ ስኬቶች የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ሥራ ውጤት ናቸው ያሉት ደግሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ስራ አስኪያጅ አቶ ተሻገር አዳሙ ናቸው።

በመጀመሪያውና 2ኛው ዙር ብቻ ስምንት ነጥብ ስድስት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ማጠናቀቅ መቻሉን ጠቁመው 3ኛው ዙርም በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።

የተቀናጀ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በማፋጠን የባሕርዳር ከተማን ሁለንተናዊ ተመራጭነት በተጨባጭ የማረጋገጥ ጉዳይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል።

በ2019 በጀት ዓመት የታቀዱ የልማት ሥራዎችን በጥራትና በፍጥነት በማከናወን የከተማዋን ህዝብ ተጠቃሚ ለማደረግ በቅንጅት እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።

በመድረኩ የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላተ ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ የመኸር አዝመራን ውጤታማ  ለማድረግ ለኩታ ገጠም እርሻና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቷል

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...

Jul 23, 2026

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026

በድሬደዋ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰዱ

ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...

Jul 21, 2026

መንግሥት የሎጂስቲክስ ዘርፉን በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...

Jul 15, 2026