የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ዘመናዊ የማሰልጠኛ እና የምርምር የላቀ ላቦራቶሪ በይፋ ስራ ጀመረ

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከተባበሩት አረብ ኢምሬቶች (UAE) መንግስት ጋር በመተባበር ያስገነባውን ዘመናዊ የማሰልጠኛ እና የምርምር የላቀ ላቦራቶሪ በይፋ ስራ አስጀምሯል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጅነር አይሻ መሐመድ፣ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጀነራል ከበደ ረጋሳ፣ የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ጀነራል መኮንኖች፣ የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ተወካዮች እንዲሁም የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል።


ላቦራቶሪው በ20 ሺህ 850 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ሲሆን፣ ለላቀ ስልጠና እና ምርምር የሚያስፈልጉ ዘመናዊ ቁሳቁሶች ሙሉ በሙሉ የተሟሉለት ነው።

በውስጡ የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣የሳይበር፣የኤሌክትሪክ ኃይል፣የአውቶሜሽን፣ የኮሙኒኬሽን እና ኤሌክትሮኒክስ እንዲሁም የነርሲንግ ሲሙሌሽን ላቦራቶሪዎችን አካቷል።

ህንፃዎች በተለየ መልኩ ዘመናዊ የሶላር የኃይል ስርዓትና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች የተገጠሙለት ነው።


ማዕከሉ የተለያዩ የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ እና የመከላከያ ምርምር ዘርፎችን በአንድ ላይ የሚያገናኝ ዘመናዊ የእውቀት ማዕከል መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

ለዩኒቨርሲቲው ወደ ተግባራዊ ምርምርና ፈጠራ ይበልጥ ለመሸጋገር ትልቅ እምርታን የሚፈጥር ነው ተብሏል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ማዕከሉ ለመከላከያ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን ለሀገሪቱ አጠቃላይ የቴክኖሎጂ፣ የኢንዱስትሪ፣የጤና እና የሳይንስ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ የመኸር አዝመራን ውጤታማ  ለማድረግ ለኩታ ገጠም እርሻና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቷል

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...

Jul 23, 2026

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026

በድሬደዋ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰዱ

ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...

Jul 21, 2026

መንግሥት የሎጂስቲክስ ዘርፉን በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...

Jul 15, 2026