የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በሀረሪ ክልል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በተሰሩ ስራዎች ውጤቶች ተመዝግበዋል

Jul 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል በተከናወኑ የግብርና ልማትን የማሳደግና ምርታማነትን የማሻሻል ስራዎች አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ ሮዛ ኡመር ገለፁ።

በተያዘው የ2019 ምርትና ምርታማነትን በማሳደግና የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ትኩረት መደረጉንም ኃላፊዋ ገልጸዋል።

ወይዘሮ ሮዛ በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በተከናወኑ ስራዎች ውጤቶች ተመዝግበዋል።

በተለይም ዓመቱን ሙሉ መልማት ከሚችሉ ምርቶች መካከል በቆሎ አንዱና ዋነኛው መሆኑን ጠቅሰው የበቆሎን ምርት በበጋና በበልግ ወቅቶች የማልማት ሥራ ሲከናወን መቆየቱን አንስተዋል።

በ2019 የበጀት አመትም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግና የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ በ2018 የበጀት አመት 2 ሺህ 160 ሄክታር መሬት በቦቆሎ መሸፈን መቻሉን ገልጸው፤ በዘንድሮው የመኸር እርሻ ወደ 2 ነጥብ 378 ሺህ ሄክታር ለማሳደግ ታቅዷል ብለዋል።

በክልሉ በተጠናቀቀው የበጀት አመት ስንዴ በሄክታር ከነበረበት 32 ኩንታል በያዝነው በጀት ዓመት ወደ 33 ኩንታል ለማሳደግ መታቀዱን ገልጸው 14 ሺህ 850 ኩንታል ይጠበቃል ብለዋል።

በተያዘው የበጀት አመት በመኸር እርሻ 11 ሺህ 956 ሄክታር መሬት በዘር እንደሚሸፈንና ከዚህ ውስጥም 2 ሺህ 378 ሄክታር መሬት በቦቆሎ ምርት የሚሸፈን መሆኑ ገልጸዋል።

በበልግና መኽር እርሻ የዝናብ እጥረትን ተቋቁመው በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጡ የማሽላ እርሻ ስራ በእጥፍ እንዲያድግና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ ይሰራል ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪም 4 ሺህ 700 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ልማት የተለያዩ የአትክልትና ስራስር ሰብሎች እንደሚሸፈን የገለጹት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሯ በከተማ ግብርናም 537 ሄክታር እንደሚሸፈን ገልጸዋል።

አርሶ አደሩ የክረምት ወቅትን ብቻ ጠብቆ ከሚሰራው የግብርና ልማት እንዲላቀቅ የግብዓት አቅርቦት፣ የመሬት ዝግጅትና የሙያተኛ አቅም ማጎልበት ሥራዎች ተከናውነዋል ነው ያሉት።

እንዲሁም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት የሚያሳድጉ ግብዓቶችን ከማቅረብ በተጨማሪ በገጠሩ አካባቢ የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር ውጤታማነት ለማሳደግ 18 የዶሮ መንደሮችን የመመስረት ስራ ይሰራል ሲሉ አብራርተዋል።

በተጨማሪም 600 ሄክታር መሬት ላይ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች እንደሚከናወኑም አብራርተዋል ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026