🔇Unmute
ሰመራ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል አፋምቦ ሐይቅ ላይ በአሳ አስጋሪነት ለተደራጁ ዜጎች የተደረገው ድጋፍ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደገው መሆኑን በዘርፉ የተሰማሩ ወጣቶች ገለጹ።
የአፋር ክልል እንስሳትና ዓሳ ሃብት ቢሮ በአፋምቦ ወረዳ በአራት ማህበራት ለተደራጁ አሳ አስጋሪዎች የቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ ወደ ስራ ማስገባቱን ገልጿል።
ተደራጅተው ወደ ስራ ከገቡት መካከል ወጣት ኢብራሂም ሁመድ እንዳለው፤ የተደረገላቸው ድጋፍ በአካባቢያቸው ለረጅም ጊዜ ጥቅም ላይ ያልዋለውን የአሳ ሀብት አልምተው ተጠቃሚ ለመሆን አስችሏቸዋል።

ይህም በማህበር ተደራጅተው በመስራት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እንዳስቻላቸው ነው የጠቆመው።
የደማአሌ አሳ አስጋሪዎች ማህበር አባል የሆነው ወጣት አብዱ በዱል በበኩሉ፤በተደረገላቸው ድጋፍ የአሳ ምርትን ለሌሎች አካባቢዎች ማቅረብ እንዳስቻላቸው ነው የገለፀው።
የገበያ ትስስርም መመቻቸቱ ጠንክሮ በመስራት ለሌሎች አርአያ እንድንሆን ያግዛል ብሏል።

የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ቢሮ ኀላፊ አቶ ኢብራሂም መሐመድ እንደተናገሩት፤ በክልሉ ባሉ ስምንት የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ሐይቆች ወጣቶችን አደራጅቶ ወደ አሳ ልማት ስራ እንዲገቡ ተደርጓል።
ለአብነትም በአፋምቦ ሐይቅ ላይ 200 ወጣቶች በዓሳ ሀብት ልማት በመሰማራት ተጠቃሚ የሚሆኑበት አሰራር መዘርጋቱን አስረድተዋል።
የክልሉ ሕብረት ስራ ማኅበራት ማደራጃና ማስፋፊያ ኤጀንሲ ኀላፊ አቶ አብዱ ሐሰን ያዬ በበኩላቸው፤ በክልሉ ወጣቶችን በማደራጀት ወደ ስራ እንዲገቡ የማድረግ ተግባራት ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።

ለዚህም ግብአትና ሙያዊ ስልጠና በመስጠት ገቢያቸውን ከማሳደግ ባለፈ ለህብረተሰቡ ጥራቱን የጠብቀ ምርት ማቅረብ እንዲችሉም አሰፈላጊው ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል ።
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...
Jul 22, 2026
ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...
Jul 21, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...
Jul 15, 2026