የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በሰሜን ሸዋ ዞን ከ177ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈን ተችሏል

Jul 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን፤ ሐምሌ 21/ 2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተያዘው ክረምት ከ177 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈን መቻሉን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በዞኑ ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ባለሙያ ወይዘሮ ሁሉምታየ ዘነበ እንደገለፁት፤ በዚህም በ2018/19 የመኸር ምርት ዘመን 563 ሺህ 336 ሄክታር መሬት በሰብል ለማልማት ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል።

ባጠቃላይ ከሚለማው ማሳ ውስጥም ከ308 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነውን በኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴ በመጠቀም በጤፍ ፣ ስንዴ ፣ ማሽላ፣ በቄላና ማሾ ሰብሎች ለማልማት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

አስካሁን በተደረገው ጥረትም 196 ሺህ 417 አርሶ አደሮችን በማሳተፍ177 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች በዘር መሸፈን መቻሉን ገልጸዋል።

የዘርፉ አመራርና ባለሙያዎችም አርሶ አደሩ የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴን፣ሌሎች የተሻሻሉ አሰራሮችንና ግብአትን ተጠቅመው በመዝራት ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

በተጨማሪም ዝናቡ ዘግይቶ በጣለባቸው አካባቢዎች ፈጥነው የሚደርሱ ሰብሎችን እንዲዘራና በማሳው ዳር እና ዳር ውሃን አቅቦ የሚያቆይ ጉድጓድ በመቆፈር እንዲጠቀም ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

በዞኑ የሞረትና ጅሩ ወረዳ አርሶ አደር የሆኑት መዝገቡ ወልዴ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ስድስት ሄክታር መሬታቸውን በኩታ ገጠም በማረስ በስንዴ፣በጤፍና በጥራጥሬ ሰብሎች ሸፍነዋል።

በአሁኑ ወቅትም ቡቃያውን መንከባከብ መጀመራቸውን ነው የተናገሩት።

ሌላው የዚሁ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ማሙሽ በቀለ በበኩላቸው፤ያለው የዝናብ ስርጭት ጥሩ በመሆኑ ሶስት ሄክታር መሬታቸውን በሰንዴ ሰብል መሸፈን መቻላቸውን አስረድተዋል።

ምርታማነታቸውን ለማሳደግም የሚያስፈልጋቸውን ማዳበሪያና ምርጥ ዘርን በወቅቱ ማግኘት በመቻላቸው ፈጥነው ወደ ዘር ስራ መግባታቸውን ተናግረዋል።

በዞኑ ከመኸር እርሻ 20 ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026