የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ለአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስኬት አስተማማኝ የልኬትና የካሊብሬሽን ሥርዓት መገንባት ወሳኝ ጉዳይ ነው - ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)

Aug 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ለአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስኬት አስተማማኝ የልኬትና የካሊብሬሽን ሥርዓት መገንባት ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።

19ኛው የአፍሪካ ሥነ-ልክ ድርጅት (ሜትሮሎጂ) ጠቅላላ ጉባዔ "ሥነ-ልክ ለዲጂታል ሽግግር፤ ተዓማኒ ልኬቶች ለአፍሪካ የወደፊት ዕጣ ፈንታ" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።


በጠቅላላ ጉባዔው የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሙሉጌታ ደርበው (ዶ/ር) እና የአፍሪካ ሥነ-ልክ ድርጅት (AFRIMETS) ፕሬዚዳንት ሔነሪ ኪበት ሮቲች (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ የዘርፉ ተወካዮች ተገኝተዋል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በአንድ የአፍሪካ ሀገር የተመረቱ ምርቶች ተደራራቢ የጥራትና የልኬት ፍተሻዎችን አልፈው ወደ ሌላ ሀገር በነፃነት እንዲዘዋወሩ የተቀናጀ የልኬት ስታንዳርድ መዘርጋት አስፈላጊ ነው።


አህጉራዊ የንግድ ትስስሩ ውጤታማ ሊሆን የሚችለውም ሀገራት ወጥና ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው የልኬት ቁጥጥር ሥርዓት ሲኖራቸው እንደሆነ አስረድተዋል።

አክለውም የሜትሮሎጂ ሥርዓትን ማዘመንና ዲጂታላይዝ ማድረግ አፍሪካ ለሰው ሠራሽ አስተውሎት እና ለላቀ ማኑፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂዎች ዝግጁ እንድትሆን እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ከመደበኛ የሥነ-ልክ ሥርዓቶች ጋር በማጣመር የላቦራቶሪ ምርመራ ውጤቶች አህጉራዊ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ማድረግ የንግድ እንቅፋቶችን እንደሚያስወግድም ጠቁመዋል።

የላቦራቶሪ ምርመራዎችንና የካሊብሬሽን አቅምን ማሳደግ የንግድ እንቅፋቶችን ከመቅረፉ ባሻገር፣ አህጉሪቱ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ሽግግር በታማኝ የልኬት መረጃ ለማስደገፍ እንደሚያስችልም አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዋ ተቋማዊ አቅምን ለማሳደግ፣ የውጭ ኢንቨስትመንት ለመሳብ እና ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየሰራች መሆኑን ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ ከቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ አጋሮች ጋር በመተባበር የሜትሮሎጂ ስታንዳርዶችን ለማጠናከርና የአፍሪካን የኢኮኖሚ ትስስር እውን ለማድረግ ሙሉ ቁርጠኝነቷን አረጋግጣለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ የመኸር አዝመራን ውጤታማ  ለማድረግ ለኩታ ገጠም እርሻና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቷል

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...

Jul 23, 2026

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026

በድሬደዋ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰዱ

ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...

Jul 21, 2026

መንግሥት የሎጂስቲክስ ዘርፉን በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...

Jul 15, 2026