🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ለሀገሪቱ የመድሀኒትና የሕክምና መገልገያዎች አቅርቦት ሰንሰለት የዘረጋው ቀልጣፋና ዘመናዊ ዲጂታል አሠራር አህጉራዊ እውቅና ማግኘቱን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ ገለጹ።
አገልግሎቱ በ5ኛው የአፍሪካ የአቅርቦት ሰንሰለት የልህቀት ሽልማት (ASCEA 2026) ከፍተኛውን የ«Gold Award» ሽልማት ማሸነፉም ተገልጿል።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ ባለፉት አራት ዓመታት በተተገበሩ መሠረታዊ የሪፎርም ሥራዎች በትኩረት አከናውኗል።
ከተከናወኑት ዋና ዋና ተግባራት መካከል አቅርቦትን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ማሸጋገር፣ የግዥ ሥርዓቱን ማዘመንና ግልጽ ማድረግ፣ የክምችትና ሥርጭት አሠራርን ማስተካከል እንዲሁም የምርቶች አቅርቦት ሰንሰለት ቅንጅትን ማጠናከር ይገኙበታል።
ይህንንም ተከትሎ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡ ሲሆን ሪፎርሙ የአገር ውስጥ የመድኃኒት አቅርቦት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያድግ ማስቻሉንም አመልክተዋል።
በተለይም ቴክኖሎጂን በመጠቀም አጠቃላይ የግዥና የክምችት ሥርዓቱን በኤሌክትሮኒክ መንገድ ማዘመን መቻሉ የአገልግሎት ቅልጥፍናን እንደጨመረው ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።
ከዚህ ቀደም ረጅም ጊዜ ይወስድ የነበሩ አሠራሮች በአጭር ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ መቻሉን አስታውቀው ይህም የደንበኞችን እርካታ በከፍተኛ ሁኔታ ከማሳደጉ ባሻገር አሠራሩን ወጪ ቆጣቢ ማድረጉንም ገልጸዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ ይህ በአገልግሎቱ የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት አህጉራዊ እውቅናም እያስገኘለት መሆኑን ጠቁመዋል።
የመድኃኒትና የሕክምና መገልገያዎች አቅርቦት ሰንሰለት የዘረጋው ቀልጣፋና ዘመናዊ ዲጂታል አሠራር አህጉራዊ ዕውቅና ያገኘ ሲሆን በቅርቡም በ5ኛው የአፍሪካ የአቅርቦት ሰንሰለት የልህቀት ሽልማት (ASCEA 2026) ከፍተኛውን የ«Gold Award» ሽልማት ማሸነፍ መቻሉንም አስታውቀዋል።
ይህ ሽልማት አገልግሎቱ የሕክምና አቅርቦት ሰንሰለቱን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ለማስደገፍና ተደራሽነቱን ለማስፋት የሠራቸው ስኬታማ ሥራዎች ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህ እውቅና ወደፊት አገልግሎቱን አህጉራዊ ተወዳዳሪና ይበልጥ ቀልጣፋ ለማድረግ ለተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ትልቅ ብርታት እንደሚሆን አክለዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026