🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ፤ ነሐሴ 28/2018(ኢዜአ)፦ የመንግሥት የፖሊሲ ማሻሻያዎችና የተቀላጠፉ አገልግሎቶች መሰጠት መጀመሩ ለኢንዱስትሪ ዘርፉ እመርታ የላቀ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ምሁራን ገለጹ።
የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ማነቆዎች በመፍታት የተሻለ እድገትና ማንሰራራት እንዲመጣ ማድረጉ ይታወቃል።
በተለይም የውጭ ምንዛሬ አቅርቦትን በማሻሻል፣ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ተኪ ምርቶች እንዲበራከቱ፣ የወጪ ንግድ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
ከዚህ በተጨማሪ ግልጽና ገበያ መር የሆነ የፋይናንስና የውጭ ምንዛሬ ስርዓት በመዘርጋቱ የውጭ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት ማድረግ እንዲችሉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።
በተለይም በማኑፋክቸሪንግና በኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች ተሳትፎ በእጅጉ እያደገ መምጣት ችሏል።
በመሆኑም በመንግስት የተወሰዱ የፖሊሲ ማሻሻያዎችና የተቀላጠፉ አገልግሎቶች በኢንዱስትሪ ዘርፉ ትልቅ እመርታ እንዲመዘገብ ያስቻሉ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገልጸዋል።
የዩኒቨርሲቲው ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ ምክትል ዲን ኢንጂነር መንግስቱ መና፤ የመንግስት የፖሊሲ ማሻሻያዎችና የተቀላጠፉ አገልግሎቶች ለኢንዱስትሪ ዘርፉ እመርታ የላቀ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን አስረድተዋል።

የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የማምረት አቅም በማሳደግ የውጭ ምንዛሬን ከማዳን በተጨማሪ ተኪ ምርቶችን በማምረት ለኢኮኖሚው መነቃቃትና ለበርካታ ዜጎችም የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉን አንስተዋል።
በዩኒቨርሲቲው የኢንዱስትሪያል አስተዳደርና ኢንጂነሪንግ ኢኮኖሚክስ መምህርና ተመራማሪ ጌታሁን ሶርሳ፤ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢንዱስትሪ ዘርፍ እየተመዘገበ ያለው ስኬት አበረታች ስለመሆኑ ገልጸዋል።

የኢንዱስትሪ መስፋፋት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በብዛትና በጥራት በማምረት የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪ መቀነስ ያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም ዘርፉ የውጭ ምንዛሪን ማዳንና ሀገራዊ የምግብ ዋስትናን በአስተማማኝ ሁኔታ ለማረጋገጥ እያገዘ በመሆኑ እነዚህን መልካም ጅምሮች ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026
ሀረር፤ ነሐሴ 20/2018 (ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል በኢንቨስትመንት ዘርፍ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ውጤታማ እያደረጋቸው መሆኑን ባለሀብቶችና ወጣቶች ገለጹ። ...
Aug 27, 2026
በሙሴ መለሰ የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በአገር በቀል የኢኮኖሚና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ታግዞ፣ ባለፉት ዓመታት የታዩበትን የአሰራርና መዋቅራዊ ችግሮች በመ...
Aug 22, 2026
ደብረብርሃን፤ ነሀሴ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር በመሳተፍ ዘላቂ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መቻላቸውን አርሶ አደሮች ገለጹ። የሌማት ት...
Aug 21, 2026