የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ ስኬት ቁርጠኛ ናት

Sep 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ ስኬት እና ለሁሉም ተሳታፊ ሀገራት ተጨባጭ ውጤት እንዲያመጣ ገንቢ ሚና ለመጫወት ቁርጠኛ መሆኗን የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ታዜር ገብረእግዚአብሔር ገለጹ።

የአፍሪካ ቀንድ ኢኒቬቲቭ የንግድ ሚኒስትሮች ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።


የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ታዜር ገብረእግዚአብሔር በዚሁ ወቅት እንዳሉት ስብሰባው የቀጣናዊ ውህደትን ወሳኝ ጠቀሜታ ያሳያል ብለዋል።

የቀጣናው ሀገራት በጂኦግራፊ፣ በታሪክ፣ በባህል እንዲሁም እየጨመረ በመጣው የጋራ የኢኮኖሚ ፍላጎት የተሳሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የበለጠ ጥልቅ የቀጣናዊ ውህደት ሂደት ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትንና የሥራ ዕድል ፈጠራን የማፋጠን መንገድ ብቻ ሳይሆን፣ የጋራ የመቋቋም አቅም እና የመረጋጋት መሠረት መሆኑን አንስተዋል።

የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጠና ራዕይን ወደ ተጨባጭ እውነታ ለመቀየር ቁልፍ መንገድ ነው ብለዋል።

ኢኒሼቲቩ ኢንቨስትመንቶችን ለማስተባበር፣ ፖሊሲዎችን ለማጣጣም እና ንግድንና ትስስርን የሚያደናቅፉ ማነቆዎችን ለመፍታት የተቀናጀ ማዕቀፍ እንደሚሆን አመላክተዋል።

በዚህ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት መንገዶች፣ ድንበሮችና የንግድ ኮሪደሮችን ከማሻሻል ባለፈ፣ መተማመንን የሚገነባ፣ ተቋማትን የሚያጠናክርና ለሕዝቦቻችን ዕድሎችን የሚፈጥር ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ ስኬት ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት እንደምትቀጥልም አረጋግጠዋል።

ለዚህም ቀጣናዊ ውህደትን በልማት ስትራቴጂ ማዕከል በማድረግ ለቀጣናዊ ኮሪደሮችና ንግድን ማመቻቸት የሚያገለግሉ መሠረተ ልማቶች ከጎረቤት ሀገራትና ከአጋሮቻችን ጋር በቅርበት በመሥራት ከፍተኛ ጥረት ማድረጓን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ከገንዘብ ድጋፍ ባለፈ ፖለቲካዊና ቴክኒካዊ ተሳትፎ እያደረገች መሆኑን ጠቅሰው፤ ኢኒሼቲቩ ለሁሉም ተሳታፊ ሀገራት ተጨባጭ ውጤት እንዲያመጣ ውይይትን በማስፋፋት፣ ፖሊሲዎችን በማጣጣምና ልምዶችን በመለዋወጥ ገንቢ ሚና ለመጫወት ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከቀጣናዊ ውህደት ዓላማዎች ጋር በቅርበት የተሳሰረ መሆኑን አመላክተዋል።


ኢትዮጵያ የንግድ ስርዓቷን እና የጉምሩክ አሠራሯን ለማዘመን፣ የንግድ ሥራ አካባቢን ለማሻሻልና ቁልፍ ተቋማትን ለማጠናከር ትልልቅ እርምጃዎችን መውሰዷን ጠቁመዋል።

በተጨማሪም የዓለም የንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቅሰው ይህም ግልጽነትንና በሕግና በደንብ የተመራ የንግድ ሥርዓትን ያጠናክራል ብለዋል።

እንዲሁም ቀጣናውን የሚያስተሳስሩ ስትራቴጂካዊ የትራንስፖርትና የሎጂስቲክስ ኮሪደሮች ላይ ኢንቨስት እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም ከቀጣናዊ ቃል ኪዳኖች ጋር የሚጣጣሙና እርስ በርስ የሚያጠናክሩ ማሻሻያዎችን ለማስፈጸም ያለንን ቁርጠኝነት ያሳያሉ ብለዋል።

የስብሰባው ተሳታፊዎች ግልጽ፣ ወደፊትን ያማከለና በዜጎች ዕለታዊ ሕይወት ውስጥ ወደ ተጨባጭ እውነታ የሚቀይሩ ተግባራዊ እርምጃዎች ላይ እንዲተኮርም ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026

በሐረሪ ክልል በኢንቨስትመንት ዘርፍ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ውጤታማ እያደረገን ነው -ባለሀብቶችና ወጣቶች

ሀረር፤ ነሐሴ 20/2018 (ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል በኢንቨስትመንት ዘርፍ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ውጤታማ እያደረጋቸው መሆኑን ባለሀብቶችና ወጣቶች ገለጹ። ...

Aug 27, 2026

የኢትዮጵያ የማዕድን ምርት እመርታ

በሙሴ መለሰ የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በአገር በቀል የኢኮኖሚና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ታግዞ፣ ባለፉት ዓመታት የታዩበትን የአሰራርና መዋቅራዊ ችግሮች በመ...

Aug 22, 2026

የሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር ዘላቂ ተጠቃሚነታችንን ለማረጋገጥ አስችሎናል-አርሶ አደሮች

ደብረብርሃን፤ ነሀሴ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር በመሳተፍ ዘላቂ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መቻላቸውን አርሶ አደሮች ገለጹ። የሌማት ት...

Aug 21, 2026