የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጥራት ደረጃውን የጠበቀ ቡና በብዛት ለማዕከላዊ ገበያ ይቀርባል

Sep 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፣ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘው በጀት አመት ቡናን በጥራት እና በብዛት አዘጋጅቶ ለማእከላዊ ገበያ ለማቅረብ ከወዲሁ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ቡናና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን ገለጸ።

ክልላዊ የቡና ምርት አሰባሰብና ተጓዷኝ ተግባራት ላይ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ዛሬ በዲላ ከተማ ተካሂዷል።


የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ አማኑኤል ብሩ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ የቡና አመራረትና ዝግጅት እየተሻሻለ በመምጣቱ ምርታማነትና ጥራትን ማሳደግ ተችሏል።

ከክልሉ በተያዘው 2019 በጀት አመት ቡናን በጥራት በማዘጋጀት በብዛት ለማእከላዊ ገበያ ለማቅረብ በየደረጃው በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በበጀት አመቱ ከ48 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማእከላዊ ገበያ እንደሚቀርብ አመላክተዋል።

ጥራት ላለው ቡና የተሻለ ዋጋ መቆረጡ የዘርፉን ተወዳዳሪነት አሳድጓል ያሉት ደግሞ የጌዴኦ ዞን የቡና ላኪዎች ማህበር ሰብሳቢ አቶ ኢያሱ ወራሳ ናቸው።


ባለፈው ዓመት ቡናን በጥራት ከማዘጋጀት ባለፈ በጊዜ ለገበያ እንዲቀርብ መደረጉ ተጠቃሚነታችን እንዲረጋገጥ አስችሏል ብለዋል፡፡

በተያዘው ምርት ዘመንም ጥራት ያለው ቡና ለገበያ ለማቅረብ ከወዲሁ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን አመልክተዋል።

ቡና ላኪ አርሶ አደር አሰለፈች ጋን በበኩላቸው የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን በመጠቀም ምርታማነትን ማሳደግ መቻላቸውን ተናግረዋል።

በተያዘው ዓመትም ከማሳቸው የሚያገኙትን የቡና ምርት በጥራት በማዘጋጀት በቀጥታ የገበያ ትስስር ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በመድረኩ አምራቾች፣ ላኪ አርሶ አደሮች፣ አቅራቢ ነጋዴዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026