🔇Unmute
አሶሳ፤ መስከረም 7/2019 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለውን የውሃ ሀብት ለመስኖ ልማት በማዋል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ የ2019 ምርት ዘመን የመስኖ እርሻ ልማት ንቅናቄ መድረክ አካሂዷል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የመስኖ ልማት ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ከተረጂነት ለመላቀቅ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ነው።
በክልሉ የመስኖ ልማት ሥራ እየተሻሻለ መምጣቱን አመልክተው፤ አርሶ አደሩም ጥቅሙን በመረዳት ከመደበኛ የግብርና ሥራ ጎን ለጎን የመስኖ ልማት ሥራን በስፋት እየተገበረ ይገኛል ብለዋል።
ከአርሶ አደሩ ባለፈ በእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሀብቶች በመስኖ እርሻ ላይ ተሰማርተው የግብርና ዘርፉን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሠሩ መሆኑን ገልጸዋል።

ክልሉ ለመስኖ ልማት ምቹ የሆነ የውሃ ሀብት ያለው በመሆኑ አነስተኛ የመስኖ ግድቦችን በመገንባት የዘርፉን ልማት የማሳደግ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው የጠቀሱት።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ባበክር ሀሊፋ በበኩላቸው፤ አርሶ አደሩ በመስኖ ልማት ስራ የሚያደርገው ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱ ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ አስችሎታል ነው ያሉት።
በተለይ በመስኖ የሚለሙ አትክልት እና ፍራፍሬዎችን ለኅብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ገበያን የማረጋጋት ሥራ ለማከናወን መቻሉንም አንስተዋል።
ባለፈው በጀት ዓመትም 57 ሺህ ሄክታር ማሳ በመስኖ በማልማት 14 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደተገኘ አመልክተው፤ በተያዘው በጀት ዓመትም 70 ሺህ ሄክታር ማሳን በመስኖ ለማልማት ወደ ሥራ መገባቱን አስታውቀዋል።
በንቅናቄ መድረኩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የዘርፉ አመራሮች እና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
አሶሳ፤ መስከረም 7/2019 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለውን የውሃ ሀብት ለመስኖ ልማት በማዋል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ተጠና...
Sep 18, 2026
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026