የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአፍሪካ ህብረት ጉባዔ የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ ለመገንባት ዝግጅት አድርገናል -በጎ ፍቃደኞች

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ታህሳስ 13/2017(ኢዜአ)፦በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባዔ የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ ለመገንባት ዝግጁ መሆናቸውን በጎ ፍቃደኞች ገለጹ።


ኢትዮጵያ 38ኛውን የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በሰለጠነ የሰው ኃይል በመታገዝ በብቃት ለማስተናገድ በቂ ዝግጅት ማድረጓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቁ ይታወሳል።


ኢትዮጵያ የህብረቱ መቀመጫና የአፍሪካ መዲና እንደመሆኗ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ በሁሉም መስክ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቋም ተገልጿል።


በጉባኤው ላይ የሚሳተፉ እንግዶችን ለማስተናገድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለዕጩና ነባር ዲፕሎማቶች እንዲሁም ለበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል።


የስልጠናው ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ እየተገነባ ያለውን የአዲስ ዓለም አቀፍ የኮንቬንሽንና ኤግዚቢሽን ማዕከል እንዲሁም የኮሪደር ልማት ስራዎችንና የተለያዩ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎችን ጎብኝተዋል።


በጎ ፍቃደኛ ወጣት ምርትነሽ ካሳሁን ለኢዜአ በሰጠችው አስተያየት በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ኢትዮጵያን የማስተዋወቅ እድል በማግኘቴ ደስተኛ ነኝ ብላለች።


በኢትዮጵያ የተፈጠረው ሠላምና መረጋጋት እንዲሁም ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ እድገት ለገጽታ ግንባታው ትልቅ ሚና እንዳለው ተናግራለች።


በጎ ፍቃደኛ ወጣት ባቻክ ኡጁሉ በበኩሉ በጉብኝቱ የተመለከተው የልማት እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ነው ያስታወቀው።


ያገኘሁት ዕድል ለአገሬ የሚጠበቅብኝን አስተዋጽኦ ለማበርከት መልካም አጋጣሚ ፈጥሮልኛል ብሏል፡፡


ከስልጠናው ባገኘሁት ዕውቀት በመታገዝ የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ በሚጠበቀው ደረጃ ለማስተዋወቅ ቁርጠኛ ነኝ ሲልም አክሏል።


በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኮንፍረንስ፣ ሁነትና የመንግሥት ፕሮቶኮል ዳይሬክተር እሸቱ ለገሰ በበኩላቸው፥ በአፍሪካ ህብረት ጉባዔ ላይ የሚሳተፉ እንግዶች ኢትዮጵያ የደረሰችበትን ደረጃ እንዲገነዘቡ የሚያስችል አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራ መከናወኑን አስታውቀዋል።


በተለያዩ ቋንቋዎች የኢትዮጵያን ገጽታ የሚያስተዋውቁ በጎ ፍቃደኞች ስልጠና በመውሰድ ላይ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡


ዛሬ የተደረገው ጉብኝት ሰልጣኞች በቂ ግንዛቤ ጨብጠው አገራቸውን እንዲያስተዋውቁ ያለመ መሆኑን ነው የገለጹት።


የውጭ ጉዳይ ኢኒስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር በረከት ድሪባ በ38ኛው የህብረቱ ጉባኤ የሚሳተፉ እንግዶች የኢትዮጵያን ገጽታ በላቀ ደረጃ እንዲረዱ በቂ ዝግጅት መደረጉን አስታውቀዋል።


በጎ ፍቃደኞቹ የውጭ ጉዳይ ዲፕሎማሲን ጨምሮ እንግዶችን ተቀብሎ በማስተናገድ ረገድ ልምድ ባላቸው አሰልጣኞች ግንዛቤ እንዲጨብጡ በመደረግ ላይ መሆኑን ነው ያስታወቁት።


ኢትዮጵያ ከኮንፍረንስ ቱሪዝም ይበልጥ እንድትጠቀም የሰለጠነ የሰው ኃይል ወሳኝ በመሆኑ መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026