የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኩታ ገጠም የቡና ልማት ውጤት አምጥቷል 

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ ሚያዝያ 20/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኩታ ገጠም የቡና ልማት የተገኘውን ስኬት ለማስፋፋት እየተሠራ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሠ መሥተዳድር እና የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) ገለጹ።

በጌዴኦ ዞን ዲላ ዙሪያ ወረዳ በሽጋዶ ቀበሌ የአረንጓዴ ዐሻራ የቡና ችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር ተከናውናል።


አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በአረንጓዴ ዐሻራ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የአፈር ለምነትን በማሻሻል በክልሉ የግብርና ምርታማነት አሳድገዋል።

በክልሉ የተጀመረው ቡናን በኩታ ገጠም የማልማት ሥራም በቡና ጥራትና ምርታማነት ላይ ውጤት ማምጣቱን ጠቅሰው፤ ተሞክሮን ለማስፋፋት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

ያረጀ የቡና ተክልን በተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች በመተካት ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ፤ ለውጭ ገበያ የሚቀርበውን የቡና መጠን ማሳደግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በተያዘው የበልግ ወቅት ከ40 ሚሊየን በላይ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች ተከላ እየተከናወነ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በምክትል ርዕሠ መሥተዳድር ማዕረግ የግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) ናቸው።


ከዚህ ውስጥ ከ5 ነጥብ 6 ሚሊየን የሚልቀው ችግኝ በኩታ ገጠም እንደሚለማ ጠቁመው፤ የቡና ጥራትና ምርታማነትን በማሻሻል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል።

በተያዘው ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃሐ-ግብር ቡናና ፍራፍሬን ጨምሮ የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው ከ32 ሚሊየን በላይ ችግኞች ተከላ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ናቸው።


የኩታ ገጠም የቡና ልማትን ለማስፋፋት በተደረገ ጥረት፤ 2 ሺህ 700 አርሶ አደሮችን በማሳተፍ ከ1 ሺህ 200 ሔክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም መልማቱን ገልጸዋል።

ዛሬ በዲላ ዙሪያ ወረዳ ሽጋዶ ቀበሌ የተካሄደው የቡና ተከላ መርሐ-ግብርም የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል።

የሽጋዶ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ዓለማየሁ ገብሬ፤ በአካባቢያቸው እየሰፋ የመጣው የኩታ ገጠም የቡና ልማት ልማዳዊ የቡና ልማትን በማስቀረት ምርታማነት እያሳደገ መሆኑን አንስተዋል።

ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በኩታ ገጠም በሚያለሙት መሬት ከ1 ሺህ በላይ የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን መትከላቸውንም አስረድተዋል።

ከቡና በተጨማሪ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚደርሱ ቦሌቄ፣ እንሰትና ሌሎች ሰብሎችን በመትከል ተጠቃሚ ለመሆን እየሠሩ መሆናቸውንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026