የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የቡና ኢንሼቲቭ ግቦችን ለማሳካት የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን የማስፋት ሥራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፣ሚያዝያ 27/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን የቡና ኢንሼቲቭ ግቦችን ለማሳካት፤ የተሻለ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን የማስፋት ሥራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ሙሐመድሳኒ አሚን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ የቡና ምርታማነትን ለመጨመር የተሻለ ምርት የሚሰጡ ችግኞች ለአርሶ አደሩ በስፋት ተደራሽ እየሆኑ ይገኛሉ።

የቡና ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ አንዱ የትኩረት አቅጣጫችን በምርምር የተሻሻሉ የቡና ዝሪያዎችን ለአርሶአደሩ በስፋት ተደራሽ ማድረግ ነው ብለዋል።

በክልሉ ለዘንድሮው የቡና ልማት በቂ የቡና ችግኞች ተዘጋጅተዋል ያሉት የቢሮው ምክትል ሃላፊ፤ በአሁኑ ወቅት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የክልሉ ዞኖችና ወረዳዎች የችግኞቹ ተከላ እየተከናወነ ይገኛል ነው ያሉት።

በዘንድሮው የቡና ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ከ200 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለመሸፈን ታቅዶ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ የችግኝ ተከላው በሳይንሳዊ ዘዴ እንዲመራ እየተደረገ መሆኑን የገለጹት ምክትል ኃላፊው፤ ለዘርፉ ባለሙያዎችና ለአርሶ አደሮች አስፈላጊው ስልጠና መሰጠቱንም ጠቁመዋል።

ምርት የማይሰጡና ያረጁ የቡና ዛፎችን የመንቀልና የተሻለ ምርት በሚሰጡ በአዲስ ዝሪያ የመተካት ስራ ከማከናወን ባለፈ የጉንደላ ስራም በስፋት መከናወኑን ተናግረዋል።

በእስካሁኑ ሂደት ያረጀና ተገቢውን ምርት የማይሰጥ ቡና በመንቀል በ66ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የተሻለ ምርት የሚሰጡ የቡና ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል።

በተመሳሳይ ባረጀ የቡና ጉንደላ ስራ ከ120ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ያለውን ተክል መሸፈን መቻሉንም ጨምረው ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት የቡና ችግኞችን በስፋት ለመትከል የሚያስችል አስተማማኝ የዝናብ ሁኔታ መኖሩን የገለጹት አቶ ሙሐመድሳኒ፤ አርሶ አደሩ በሙሉ አቅሙ ተከላውን በማከናወን ጊዜውን በአግባቡ እንዲጠቀም ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ በዘንድሮው ዓመት 16 ሚሊዮን ኩንታል የቡና ምርት መሰብሰቡን የገለፁት አቶ ሙሐመሳኒ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 251 ሺህ ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡንም ጨምረው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026