🔇Unmute
አሶሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የግብርናውን ዘርፍ በምርምር በመደገፍ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ አሰራሮች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ገለጸ።
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ባካሄደው 11ኛው ዓመታዊ የምርምር ኮንፍረንስ ላይ የኢትዮጵያ ግብርና ኢንስትቲዩት በምርምር የታገዙ የግብርና ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፍ አብራርተዋል።
ኢንስቲትዩቱ የየአካባቢውን ስነ ምህዳር የሚላመዱ እና በምርምር የተደገፉ የግብርና ውጤቶች ለአርሶአደሩ በሰርቶ ማሳያ መልክ እንዲቀርቡ በማድረግ ላይ መሆኑንም ዶክተር ፍሬው ተናግረዋል።
አርሶአደሩ የእርሻ ማሳውን በቴክኖሎጂ ታግዞ በስፋት እንዲያለማ በማድረግና የግብርናው ዘርፍ ገበያ ተኮር እንዲሆን በተከናወነው ስራም የአርሶአደሩ ህይወት እየተሻሻለ መምጣቱን ገልጸዋል።
ኢንስቲትዩቱ በሁሉም አካባቢዎች በፈጠራ የታገዙ የግብርና ፕሮጀክቶችን ለማከናወን የሚያስችል ማዕከላትን በመክፈት በተለያዩ የሰብል አይነቶችና የእንስሳት ዝርያዎች ላይ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል።
በተለይም በቅርቡ ተግባራዊ የተደረገው የግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታ የግብርናው ዘርፍ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚጠበቅበትን ሚና እንዲወጣ የሚያደርግ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ የምርምር ተቋማት እና የግብርናው ዘርፍ አጋር አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አስታውቀዋል።
በግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታው ተጠቃሚ ከሚሆኑት አካባቢዎች አንዱ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሆኑን የተናገሩት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ ፍኖተ ካርታው በክልሉ እየተከናወነ ያለውን የግብርና ስራ የበለጠ ውጤታማ በማድረግ የአርሶአደሩን ተጠቃሚነት እና ምርታማነት እንደሚያሳድግ አብራርተዋል።
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ የሚገኘው የምርምር ስራም ለሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተሞክሮነት የሚጠቀስ መሆኑን ዶክተር ፍሬው ጠቅሰዋል።
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...
Jul 29, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...
Jul 29, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...
Jul 16, 2026
መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...
Jul 10, 2026