የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የቱሪዝም ሀብቶችን ለይቶ ጥቅም ላይ ለማዋል የተሰሩ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት አምጥተዋል

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ያሉ የቱሪዝም ሀብቶችን በመለየት፣ በማልማትና ለጎብኚዎች ምቹ በማድረግ ረገድ በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።

ባለፉት ዓመታት የለውጡ መንግስት እንደ ሀገር ተግባራዊ ያደረገው የብዝሃ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ግንባታ ፖሊሲ በኢትዮጵያ ለዓመታት ሳይታወሱና ሳይለሙ የቆዩ እምቅ የተፈጥሮና የሰው ሰራሽ ጸጋዎችን አውጥቶ ጥቅም ላይ ለማዋል አስችሏል።

የተፈጥሮ ጸጋዎችን ለማልማት በተከናወኑ የተቀናጁ ተግባራትም ተጨባጭና ስኬታማ ውጤት እየተመዘገበ ነው።

ኢኮኖሚውን ከአንድ ዘርፍ ጥገኝነት ለማውጣት በተነደፈው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ዕቅድ ውስጥ ቱሪዝም አንዱና ዋናው የኢኮኖሚ ምሶሶ ተደርጎ ትኩረት ተሰጥቶታል።

በሀገሪቱ ዕምቅ የቱሪዝም ሀብቶች ከሚገኙባቸው አካባቢዎች መካከል ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዱ ሲሆን ክልሉ ሀብቶቹን ወደ ውጤት በመቀየር ረገድ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን በማስመልከት ኢዜአ ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ርዕስ መስተዳድሩ አቶ ጥላሁን ከበደ እንዳሉት፤ በክልሉ የሚገኙ ዕምቅ የቱሪዝም ሀብቶች ተለይተው እንዲተዋወቁና የልማቱ አካል እንዲሆኑ ሀገራዊ ለውጡ ምቹ መደላድል ፈጥሯል።

ቀደም ሲል ለቱሪዝም ዘርፍ ብዙም ትኩረት ባለመሰጠቱ ኢኮኖሚያዊ አስተዋፅኦው የጎላ እንዳልነበር አስታውሰው፣ ለውጡን ተከትሎ በተሰጠ ትኩረት በክልሉ ያሉ የቱሪስት ሀብቶችን ለይቶ የማልማትና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የማሳደግ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል።

እንደ ሀገር ለቱሪዝም ዘርፍ እየተሰጠ ያለው ትኩረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣት በክልሉ የቱሪዝም ልማት ላይም የራሱን አበርክቶ ማድረጉን አቶ ጥላሁን ገልጸዋል።

በክልሉ የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ እሴቶች እንዲሁም ሀይማኖታዊና ታሪካዊ ስፍራዎች እንዳሉ ገልጸው፣ እነዚህ የቱሪዝም ሀብቶች ለኢኮኖሚው እድገት አስተዋፅኦ እንዲኖራቸው በልዩ ትኩረት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል።

በዚህም በክልሉ ከዘርፉ የሚገኘው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ መምጣቱን ጠቁመው፣ በቀጣይም ይህን ውጤት በማስቀጠል የዘርፉን ፋይዳ ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል።

እንደ ርዕሰ መስተዳድሩ ገለጻ፣ በክልሉ የመስህብ ስፍራዎችን የማልማትና የማስተዋወቅ እንዲሁም የመጠበቅ ሥራዎች በቅንጅት እየተከናወኑ ሲሆን ይህም የጎብኚዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር አድርጓል።

ባለሀብቶችም ትልልቅ ሆቴሎችን ጨምሮ ደረጃቸውን የጠበቁ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን በመገንባት በቱሪዝም ዘርፉ ክልሉም ሆነ ሀገር ተጠቃሚ እንዲሆኑ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ ያለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ ያሉ የቱሪስት መስህቦችን ከጎበኙ ከ43 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገር ጎብኚዎች 480 ሚሊዮን ብር ገቢ መገኘቱንም ለማወቅ ተችሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026