🔇Unmute
ሀዋሳ፤ ግንቦት 12/2018 (ኢዜአ)--በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪውን ምርታማነት ማሳደግ እንደተቻለ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ አስታወቀ።
የመመሪያው ሃላፊ አቶ በሀይሉ ጌታቸው ለኢዜአ እንደገለጹት በከተማው የአምራች ኢንዱስትሪውን ምርታማነት ለማሳደግ ከሀይል አቅርቦት ጋር የሚነሱ ችግሮችንና መሰረተ ልማቶች ለማሟላት በተቀናጀ መንገድ ተሰርቷል፡፡
በዚህም በበጀት ዓመቱ እስካሁን ድረስ 70 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ በመግባት ከ9 ሺህ 800 በላይ ለሚሆኑ ዜጎችም የሥራ ዕድል መፈጠራቸውን ተናግረዋል።
ኢንዱስትሪዎች ምርቶቻቸውን የሚያስተዋውቁበትና የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበትን ኤግዚብሽንና ባዛሮችን በማዘጋጀት ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉንም ነው አቶ በሀይሉ አመልክተዋል።

የአብርሽና ቤተሰቡ የቆዳና ቆዳ ውጤቶች አምራች ኢንዱስትሪ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ከድር አህመድ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኢንዱስትሪው እየገጠሙት ያሉትን ችግሮች በተቀናጀ መልኩ ለመፍታት እያስቻለ መሆኑን ጠቁመዋል።
በአስተዳደሩ በኩል የድጋፍና ክትትል ሥርዓት በመጠናከሩ የዓለም አቀፍ ገበያን ደረጃ የሚያሟሉ የቆዳ ምርቶች እያመረቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሀይል አቅርቦት ችግር እየተፈታ መምጣትና ለኢንዱስትሪዎች በተለያያ መንገድ የገበያ ትስስር መፈጠሩ ለውጤታማነቱ የላቀ ድርሻ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡
እንደ አቶ ከድር ገለጻ ኢንዱስትሪው በአሁኑ ወቅት ካፒታሉን ወደ 9 ሚሊዮን ብር ያሳደገ ሲሆን ለ107 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ችሏል።

የኦሱ ማሽነሪ ፈጠራዎች ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ወጣት በረከት ሀይሉ በበኩሉ ከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪዎችን ማበረታታቱ የማህበረሰቡን ኑሮ የሚያሻሽሉ የተለያዩ ማሽኖችን በማምረት ለገበያ እንዲያቀርቡ ያገዛቸው መሆኑን ተናግሯል።
በዚህም ድርጅቱ ካፒታሉን እያሳደገ ከመምጣቱ ባለፈ ለ15 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል።
በመንግስት በኩል የቀረበላቸው የመስሪያና የመሸጫ ቦታ እንዲሁም አስተማማኝ የሀይል አቅርቦት መኖሩ ስራቸውን ውጤታማ ማድረጉንም ተናግረዋል።
ይህም ድርጅቱ ከውጭ የሚገቡ ማሽኖችን በማምረት በአነስተኛ ዋጋና በላቀ ጥራት ለገበያ ለማቅረብ አንዳስቻለው ጠቁመዋል።
የህብረተሰቡ የሀገር ውስጥ ምርቶችን የመጠቀም ባህል እየጎለበተ መምጣቱም ሥራቸውን ለማሳደግ ብርታት እንደሆናቸው ገልጿል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026