የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ውጤታማነታቸውን የማረጋገጡ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል

May 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ፤ ግንቦት 18/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ውጤታማነታቸውን የማረጋገጡ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ተናገሩ።


ርዕሰ መስተዳድሩ ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባውን የአርባ ምንጭ "ያላ አግሮ ኢንዱስትሪ"ን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።


ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በምረቃ መርሃግብሩ ላይ እንዳሉት፤ በክልሉ የልማት ጸጋዎችን ለይቶ እሴት ጨምሮ ለማምረት የኢንዱስትሪ ዘርፉን አቅም ማሳደግ ይገባል።


ለዚህም አምራች ኢንዱስትሪዎችን በተለያየ መንገድ በመደገፍ እሴት ጨምረው ለገበያ እንዲያቀርቡና ለአርሶ አደሩም የግብይት አማራጭ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።


ዛሬ ወደሥራ የገባው ያላ ወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ክልሉ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ለማበረታታት የሚሰራው ተግባር ውጤታማነት ማሳያ መሆኑንም ተናግረዋል።


በክልሉ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ውጤታማነታቸውን የማረጋገጡ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።


እንደ አቶ ጥላሁን ገለጻ፤ በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን ለመሳብ የተቀናጀ ሥራ ከማከናወኑ ባለፈ የአርሶ አደሩን ምርታማነት የሚያሳድጉ የእንስሳት ዝርያን የማሻሻል፣ የእንስሳት ጤናን የመጠበቅ እንዲሁም የእንስሳት መኖ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።


የክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጥላሁን ብርሃኑ በበኩላቸው፤ በክልሉ ያላ የወተት አግሮ ኢንዱስትሪን ጨምሮ 142 አምራች ኢንተርፕራይዞች አሉ።


ኢንዱስትሪ ፓርኮቹ እሴት በመጨመርና ተኪ ምርቶችን በማምረት የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለሚደረገው ጥረት እያገዙ መሆናቸውንም አንስተዋል።


ይህን በማጠናከር ለሀገር ዕድገት እና ለዜጎች ተጠቃሚነት የአምራች ኢንዱስትሪ ሚና ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ ነው ሲሉም አክለዋል።


የያላ አግሮ ኢንዱስትሪ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ አለማየሁ እስራኤል፤ ኢንዱስትሪው በቀን 24 ሺህ ሊትር ጥራት ያለው ወተት ማቀነባበር እንደሚችል ገልጸዋል።


ለ150 ዜጎች ቀጥተኛ የሥራ ዕድል የሚፈጥር ሲሆን፤ በእሴት ሰንሰለት ከ5 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አስረድተዋል።


ኢንዱስትሪው ፓስቸራይዝድ ወተት፣ ተፈጥሯዊ እርጎ፣ ቺዝ፣ ክሬም እና አይብ እንደሚያመርትም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026