🔇Unmute
አርባ ምንጭ፤ ግንቦት 18/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ውጤታማነታቸውን የማረጋገጡ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ተናገሩ።
ርዕሰ መስተዳድሩ ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባውን የአርባ ምንጭ "ያላ አግሮ ኢንዱስትሪ"ን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በምረቃ መርሃግብሩ ላይ እንዳሉት፤ በክልሉ የልማት ጸጋዎችን ለይቶ እሴት ጨምሮ ለማምረት የኢንዱስትሪ ዘርፉን አቅም ማሳደግ ይገባል።
ለዚህም አምራች ኢንዱስትሪዎችን በተለያየ መንገድ በመደገፍ እሴት ጨምረው ለገበያ እንዲያቀርቡና ለአርሶ አደሩም የግብይት አማራጭ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
ዛሬ ወደሥራ የገባው ያላ ወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ክልሉ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ለማበረታታት የሚሰራው ተግባር ውጤታማነት ማሳያ መሆኑንም ተናግረዋል።
በክልሉ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ውጤታማነታቸውን የማረጋገጡ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
እንደ አቶ ጥላሁን ገለጻ፤ በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን ለመሳብ የተቀናጀ ሥራ ከማከናወኑ ባለፈ የአርሶ አደሩን ምርታማነት የሚያሳድጉ የእንስሳት ዝርያን የማሻሻል፣ የእንስሳት ጤናን የመጠበቅ እንዲሁም የእንስሳት መኖ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
የክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጥላሁን ብርሃኑ በበኩላቸው፤ በክልሉ ያላ የወተት አግሮ ኢንዱስትሪን ጨምሮ 142 አምራች ኢንተርፕራይዞች አሉ።

ኢንዱስትሪ ፓርኮቹ እሴት በመጨመርና ተኪ ምርቶችን በማምረት የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለሚደረገው ጥረት እያገዙ መሆናቸውንም አንስተዋል።
ይህን በማጠናከር ለሀገር ዕድገት እና ለዜጎች ተጠቃሚነት የአምራች ኢንዱስትሪ ሚና ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ ነው ሲሉም አክለዋል።

የያላ አግሮ ኢንዱስትሪ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ አለማየሁ እስራኤል፤ ኢንዱስትሪው በቀን 24 ሺህ ሊትር ጥራት ያለው ወተት ማቀነባበር እንደሚችል ገልጸዋል።
ለ150 ዜጎች ቀጥተኛ የሥራ ዕድል የሚፈጥር ሲሆን፤ በእሴት ሰንሰለት ከ5 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አስረድተዋል።

ኢንዱስትሪው ፓስቸራይዝድ ወተት፣ ተፈጥሯዊ እርጎ፣ ቺዝ፣ ክሬም እና አይብ እንደሚያመርትም ተናግረዋል።
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...
Jul 29, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...
Jul 29, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...
Jul 16, 2026
መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...
Jul 10, 2026