🔇Unmute
አርባ ምንጭ፤ ሰኔ 2/2018 (ኢዜአ)፡-በአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው ያሉ የቱሪስት መዳረሻዎችን ከጎበኙ የሀገር ወስጥና የውጭ ቱሪስቶች ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የከተማው ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ።
ከተማዋን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራትም ውጤት መመዝገቡ ተመላክቷል።
የአርባ ምንጭ ከተማ ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ደስታ ደምበላ ለኢዜአ እንደተናገሩት በከተማው አርባ ምንጮች፣ ዓባያና ጫሞ ሐቆችን፣ የነጭ ሣር ብሔራዊ ፓርክ፣ አዞ ራንችና ሌሎች መዳረሻዎች በስፋት ይገኛሉ።

ቱሪስቶች የሚያርፉባቸው ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሪዞርቶች፣ ሎጆችና ሆቴሎች መኖራቸውን የጠቀሱት አቶ ደስታ በበጀት ዓመቱ ብቻ አራት ዓለም አቀፍ ሆቴሎች ተገንብተው ለአገልግሎት በቅተዋል።
በበጀት ዓመቱ እስካሁን ድረስ ከ320 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ከተማዋን እንደጎበኙና ከዚህም ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ተናግረዋል።
በአርባ ምንጭ ከተማ ተጨማሪ የቱሪስት መዳረሻዎች እየለሙ መሆናቸው ገልጸው፣ በዚህም ከጋሞ ልማት ማህበር ጋር በመቀናጀት የተከናወኑ ተግባራት ከተማዋን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል እያደረጋት ይገኛል ብለዋል።

የጋሞ ልማት ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ማንደፍሮት ዱባለ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንደገለጹት ልማት ማህበሩ በበጀት ዓመቱ በዓባያ ሐይቅ ላይ የሚገኙ 11 ደሴቶችን የሚያስተሳስር የጀልባ ትራንስፖርት አገልግሎት ጀምሯል።
በከተማው ግርጌ በአንድ ስፍራ የሚገኙ 40ዎቹ ምንጮችን ለመመልከት ለሚመጡ ቱሪስቶች ምቹ ሁኔታ ለመፍጠርም "አርባ ፤ አርባ ሁለት" የተሰኘ 1ሺህ 680 ደረጃ ያለው መንገድ መገንባቱን ገልጸዋል።
ለጉብኝት ወደ አርባ ምንጭ ከተማ ከመጡ ቱሪስቶች መካከል ከአዲስ አበባ እንደመጣ የተናገረው ወጣት ታደለ ግዛት በከተማዋ የተለያዩ መዳረሻዎችን መጎብኘቱን ተናግሯል።

አርባ ምንጭን ጨምሮ በሀገራችን ሊጎበኙ የሚገባቸው ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊና ባህላዊ ሀብቶች እንዳሉ ገልጾ፣ ኢትዮጵያውያን እነዚህን የቱሪዝም ሀብቶች የመጎብኘትና የማወቅ ባህል ልናዳብር ይገባል ብሏል።
አርባ ምንጭና አካባቢዋ ልዩ የተፈጥሮ ሀብት የተቸረ በመሆኑ ቀልብን ይማርካል ያለው ደግሞ ከፖላንድ የመጣው ጎብኚ ሚስተር ባርተክ ሮማን ነው።
በአርባ ምንጭና አካባቢው የሚገኙ 40 ዎቹ ምንጮች፣ ነጭ ሣር ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም ዓባያና ጫሞ ሐይቆችን በመመልከት መደሰቱን ገልጿል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026