የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የወልድያ ሕዝብና አመራር ለፈተና ሳይበገሩ ከተማዋን ወደ ዘመናዊ የልማት ማዕከልነት እየቀየሩ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

Jun 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ የወልድያ ከተማ ሕዝብና አመራር ሰው ሠራሽ ፈተናዎችን በጽናት በመቋቋም ከተማዋን ወደ ዘመናዊ የልማት ማዕከልነት መቀየር መቻላቸውን የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ ይህንን የገለጹት በወልድያ ከተማ የተገነቡ ልዩ ልዩ የልማት ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በበቁበት መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።

ርዕሰ መስተዳድሩ ከተማዋ የጀግኖች ታሪክ የሚዘከርባት፣ ሕብረ-ብሔራዊ ወንድምና እህት ሕዝቦች በፍቅርና በአንድነት የሚኖሩባት የኢትዮጵያዊነት መገለጫ መሆኗን ገልጸዋል።


ከተማዋ በተደጋጋሚ ያጋጠሟትን ፈተናዎች ተቋቁማ፣ በአንድ እጇ ሰላምን በሌላ እጇ ልማትን ይዛ መጓዟን አብራርተዋል።

ዛሬ የተመረቁ የልማት ፕሮጀክቶች የወልድያ ከተማን ገጽታ የቀየሩ መሆናቸውን ነው ርዕሰ መስተዳድሩ የጠቀሱት።

ታዳጊዎች ስለ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እና ስለ ወደፊት ቴክኖሎጂ ያላቸው የእውቀት መሻት ከተማዋ ለነዋሪዎቿ ምቹ ከመሆን ባለፈ ራዕይ ያላቸው ዜጎችን ለመቅረጽ እየሠራች መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል።

ይህ በፈተና ውስጥ ሆኖ የመሥራት ልምድ ሌሎች የክልሉ ከተሞችና ወረዳዎች ሊማሩበትና የሥራ መነሻ ሊያደርጉት የሚገባ መሆኑን በአጽንኦት ጠቅሰዋል።

ወልድያ ገና ብዙ ልማት እንደሚገባትና በአራቱም አቅጣጫዎች ለንግድ ምቹ የሆነ ስትራቴጂካዊ አቀማመጧን ታሳቢ ያደረገ ጉዞን ማፋጠን እንደሚገባም አንስተዋል።

በሼህ መሐመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ የተገነባው ዘመናዊ ስታዲየም ከፍተኛ እድሳት እንደሚፈልግና ከተማዋን የስፖርትና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ ለስታዲየሙ የሚመጥኑ ዘመናዊ ሆቴሎች ሊገነቡ እንደሚገባ አመላክተዋል።

የከተማዋን ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ ከተቻለ ከዚህ የላቀ ልማት ማምጣት እንደሚቻልም ገልጸዋል።


​የወልድያ ከተማ ከንቲባ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፤ ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹና ፅዱ ማድረግ ያስቻሉ አስደናቂ የልማት ሥራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።

የወልድያ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የከተማዋ ነዋሪዎች ፈጣን የመንግሥት አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር የሚፈጥር መሆኑን አስረድተዋል።

በልማት ፕሮጀክቶች ምረቃ መርሃ ግብሩ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026