የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የተጀመሩ የልማት ስራዎች እንዲፋጠኑ የምናደርገውን ተሳትፎ አጠናክረን እንቀጥላለን-ወጣቶች

Jun 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ከአሸናፊው ፓርቲ ጎን በመቆም የአካባቢያችንን ሰላም በመጠበቅ የተጀመሩ የልማት ስራዎች እንዲፋጠኑ የምናደርገውን ተሳትፎ አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የአምቦ ከተማ ወጣቶች ገለጹ።

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሕዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤቶች ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን መቀመጫ በማግኘት ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአምቦ ከተማ ወጣቶች፤ የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የተጀመሩ የልማት ስራዎች እንዲፋጠኑ ከአሸናፊው ፓርቲ ጎን በመሆን የሚያደርጉትን ተሳትፎ እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወጣት ሽብሩ ነገሪ፤ ብልጽግና ፓርቲ የሕዝቡን ጥያቄ መፍታት የሚችሉና ቀደም ሲል በሀገርና በክልል ደረጃ የተጀመሩ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል አለበት ብሏል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የታቀዱ ግዙፍ የልማት ስራዎች እንዲሳኩ ከፓርቲው ጎን በመሆን የበኩሉን እንደሚወጣ ገልጿል።

በከተማዋ በሁሉም ዘርፎች እየተካሄዱ ያሉ የልማት ሥራዎችን ለማገዝ መዘጋጀቱን የገለጸው ደግሞ ወጣት ዮሐንስ ሚደቅሳ ነው።

ከአሸናፊው ፓርቲ ጋር በመሆን በተጀመሩ የልማት ሥራዎች ላይ በመሳተፍ እንዲሁም የአካባቢውን ወጣቶች በማስተባበር የሚጠበቅበትን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።

ወጣት ጭምዴሳ ነገሪ በበኩሉ፤ አብላጫ የምክርቤት መቀመጫ ያገኘው ፓርቲ ከዚህ ቀደም ዜጎች ሲያነሷቸው የነበሩ የልማት ጥያቄዎችን መመለስ ይጠበቅበታል ብሏል።

የተጀመሩና የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ፕሮጀክቶች እንዲቀጥሉ የበኩሉን እንደሚወጣም ገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026