🔇Unmute
ጋምቤላ ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የገቢ አቅምን በማሳደግ የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶችን ለማሳካት ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ።
በክልሉ የገቢ እቅድ አተገባበር ዙሪያ የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የውይይት መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ኡማን አሙሉ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፤ ክልሉ የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የታለሙትን የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶች ለማሳካት ትኩረት ተሰጥቷል።
ለእቅዱ ስኬታማነት የዘርፉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነት የላቀ ድርሻ ያለው መሆኑን አስገንዝበዋል።
የግብር አሰባሰብ ሂደቱ ፍትሃዊ፣ ግልጽና ዘመናዊ አሰራርን የተከተለ እንዲሆን በትጋት እንደሚሰራ አመላክተዋል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ቸንኮት ዴቪድ በበኩላቸው፤ በክልሉ ያለውን የገቢ አቅም በአግባቡ ለመሰብሰብና ለመጠቀም አዳዲስ አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።
የውይይት መድረኩ ዋና ዓላማም በአዳዲስ አሰራሮች ላይ የሚመለከታቸው አካላት በቂ ግንዛቤ ይዘው እንዲሰሩ ማስቻል መሆኑን አስታውቀዋል።
በክልሉ ባለፉት 11 ወራት ከ4 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተመላክቷል።
ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...
Jun 23, 2026
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026