የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የክልሉን የገቢ አቅም በማሳደግ የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶችን ለማሳካት ትኩረት ተሰጥቷል

Jun 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የገቢ አቅምን በማሳደግ የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶችን ለማሳካት ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ።

በክልሉ የገቢ እቅድ አተገባበር ዙሪያ የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የውይይት መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።


የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ኡማን አሙሉ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፤ ክልሉ የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የታለሙትን የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶች ለማሳካት ትኩረት ተሰጥቷል።

ለእቅዱ ስኬታማነት የዘርፉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነት የላቀ ድርሻ ያለው መሆኑን አስገንዝበዋል።

የግብር አሰባሰብ ሂደቱ ፍትሃዊ፣ ግልጽና ዘመናዊ አሰራርን የተከተለ እንዲሆን በትጋት እንደሚሰራ አመላክተዋል።


የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ቸንኮት ዴቪድ በበኩላቸው፤ በክልሉ ያለውን የገቢ አቅም በአግባቡ ለመሰብሰብና ለመጠቀም አዳዲስ አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።

የውይይት መድረኩ ዋና ዓላማም በአዳዲስ አሰራሮች ላይ የሚመለከታቸው አካላት በቂ ግንዛቤ ይዘው እንዲሰሩ ማስቻል መሆኑን አስታውቀዋል።

በክልሉ ባለፉት 11 ወራት ከ4 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026