🔇Unmute
ጋምቤላ ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የገቢ አቅምን በማሳደግ የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶችን ለማሳካት ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ።
በክልሉ የገቢ እቅድ አተገባበር ዙሪያ የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የውይይት መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ኡማን አሙሉ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፤ ክልሉ የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የታለሙትን የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶች ለማሳካት ትኩረት ተሰጥቷል።
ለእቅዱ ስኬታማነት የዘርፉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነት የላቀ ድርሻ ያለው መሆኑን አስገንዝበዋል።
የግብር አሰባሰብ ሂደቱ ፍትሃዊ፣ ግልጽና ዘመናዊ አሰራርን የተከተለ እንዲሆን በትጋት እንደሚሰራ አመላክተዋል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ቸንኮት ዴቪድ በበኩላቸው፤ በክልሉ ያለውን የገቢ አቅም በአግባቡ ለመሰብሰብና ለመጠቀም አዳዲስ አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።
የውይይት መድረኩ ዋና ዓላማም በአዳዲስ አሰራሮች ላይ የሚመለከታቸው አካላት በቂ ግንዛቤ ይዘው እንዲሰሩ ማስቻል መሆኑን አስታውቀዋል።
በክልሉ ባለፉት 11 ወራት ከ4 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተመላክቷል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026