የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የመስኖ መሰረተ ልማት ውጤታማነት የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ስኬታማ ጉዞ እየገነባ ነው

Jun 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦የመስኖ መሰረተ ልማት ውጤታማነት በግብርና ዘርፍ የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ስኬታማ ጉዞ እየገነባ መሆኑን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ አብዱረህማን አብደላ ገለጹ።

የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ከክልል መስኖ ቢሮ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በውስጥ ስታንዳርድ ዝግጅትና ትግበራ ዙሪያ የልምድ ልውውጥ መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ አብዱረህማን አብደላ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በጥራትና ፍጥነት በማጠናቀቅ የልማት አቅም እንዲሆኑ እየተደረገ ነው።

የመስኖ መሰረተ ልማት ውጤታማነትን ለማሻሻልም በስታንዳርድ መምራት የሚያስችሉ በርካታ የአሰራር ሥርዓቶች ተዘጋጅተው ስራ ላይ እንዲውሉ መደረጉን ገልጸዋል።

የስታንዳርድ የአሰራር ሥርዓቶችም በፌደራልና የክልል መንግሥታት የሚከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎችን በተደራጀ መልኩ እንዲመሩ በማስቻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በሀገር አቀፍ ደረጃ በተቀናጀ አግባብ የሚከናወኑ የመሰረተ ልማት ሥራዎች የመስኖ ልማት ሽፋንን በማሳደግ በምርታማነት ዕድገት ላይ ወሳኝ ሚና እየተወጡ ነው ብለዋል።

በመስኖ መሰረተ ልማት ውጤታማነትም የበጋ መስኖ ስንዴን ጨምሮ በሁሉም ዘርፍ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ አስደናቂ ውጤት እየተገኘ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም ከውጭ የሚገቡ የግብርና ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ስኬታማ ጉዞን እያፋጠነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን የግብርና ልማት ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ በሁሉም ወቅቶች የማምረት ስራ ባህል ሆኖ እንዲቀጥል በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ፋውንዴሽኑ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች ድጋፍ እያደረገ ነው

ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...

Jun 23, 2026

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026