🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦የመስኖ መሰረተ ልማት ውጤታማነት በግብርና ዘርፍ የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ስኬታማ ጉዞ እየገነባ መሆኑን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ አብዱረህማን አብደላ ገለጹ።
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ከክልል መስኖ ቢሮ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በውስጥ ስታንዳርድ ዝግጅትና ትግበራ ዙሪያ የልምድ ልውውጥ መድረክ እያካሄደ ይገኛል።
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ አብዱረህማን አብደላ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በጥራትና ፍጥነት በማጠናቀቅ የልማት አቅም እንዲሆኑ እየተደረገ ነው።
የመስኖ መሰረተ ልማት ውጤታማነትን ለማሻሻልም በስታንዳርድ መምራት የሚያስችሉ በርካታ የአሰራር ሥርዓቶች ተዘጋጅተው ስራ ላይ እንዲውሉ መደረጉን ገልጸዋል።
የስታንዳርድ የአሰራር ሥርዓቶችም በፌደራልና የክልል መንግሥታት የሚከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎችን በተደራጀ መልኩ እንዲመሩ በማስቻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በሀገር አቀፍ ደረጃ በተቀናጀ አግባብ የሚከናወኑ የመሰረተ ልማት ሥራዎች የመስኖ ልማት ሽፋንን በማሳደግ በምርታማነት ዕድገት ላይ ወሳኝ ሚና እየተወጡ ነው ብለዋል።
በመስኖ መሰረተ ልማት ውጤታማነትም የበጋ መስኖ ስንዴን ጨምሮ በሁሉም ዘርፍ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ አስደናቂ ውጤት እየተገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም ከውጭ የሚገቡ የግብርና ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ስኬታማ ጉዞን እያፋጠነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን የግብርና ልማት ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ በሁሉም ወቅቶች የማምረት ስራ ባህል ሆኖ እንዲቀጥል በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...
Jun 23, 2026
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026