🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተሞች የኮሪደር ልማትና ሌሎች ፕሮጀክቶች ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ እድል መፍጠራቸውን የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊዎች ገለጹ፡፡
በአዲስ አበባ ተጀምሮ የከተማ ገጽታን በመቀየርና የነዋሪዎችን ህይወት በማዘመን ረገድ አንጸባራቂ ውጤት የተመዘገበበት የኮሪደር ልማት አሁን ላይ ወደ ክልል ከተሞች ተስፋፍቶ ቀጥሏል፡፡
በአዲስ አበባ እንደታየው ሁሉ በክልል ከተሞች የተሽከርካሪና የእግረኛ መንገዶች፣ የብስክሌት መስመሮች፣ የንግድና የሕዝብ መዝናኛ ሥፍራዎች ደረጃቸውን ጠብቀው ተገንብተዋል፡፡
ይህም ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድልን የፈጠረው የልማት ሥራ የከተሞችን ውበት እና ለኑሮ ያላቸውን ምቾት በእጅጉ እየጨመረው ይገኛል።

የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተሞች የተከናወኑ እና በመከናወን ላይ ያሉ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለወጣቱ ሰፊና ዘላቂ የሥራ እድል መፍጠር ችለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራ እና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አስፋው ለገሰ፤ ኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሜጋ ፕሮጀክቶች በርካታ ዜጎችን በሥራ ዕድልና በንግድ ሥራ ተጠቃሚ ማድረጋቸውን አንስተዋል።

በከተማዋ በተከናወኑ የወንዝ ዳርቻ ልማት፣ የፓርኮች ግንባታ እና የቤት ልማት ፕሮጀክቶች ከፍተኛ ቁጥር ላላቸው ወጣቶች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ጠቁመዋል፡፡
ቢሮው በ2018 በጀት ዓመት እስካሁን ድረስ ከ365 ሺህ በላይ ዜጎች በተለያዩ መስኮች ወደ ሥራ መሰማራታቸውን ተናግረዋል፡፡
በከተማዋ ኢንዱስትሪ፣ ኮንስትራክሽን፣ የከተማ ግብርና፣ አገልግሎት በስፋት የሥራ ዕድል የተፈጠረባቸው የሥራ መስኮች መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡

የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው፣ ከተማ አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ እስካሁን ለ19 ሺህ 642 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል፡፡

ለዚህም በከተማዋ የተከናወኑ እና በመከናወን ላይ ያሉ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ጉልህ ድርሻ ማበርከታቸውን ተናግረዋል፡፡
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026