የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የተማሪዎችን የፈጠራ ተነሳሽነትና አቅም በሞራልና በቁሳቁስ መደገፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነት ሊሆን ይገባል

Jun 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦የተማሪዎችን የፈጠራ ተነሳሽነትና አቅም በሞራልና በቁሳቁስ መደገፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) ገለጹ።

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ክልላዊ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይና የጥናትና ምርምር ሲምፖዚየም በባህር ዳር ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።

በወቅቱም ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የተማሪዎችን የፈጠራ ተነሳሽነትና አቅም በሞራልና በቁሳቁስ መደገፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነት ሊሆን ይገባል።


ወጣት ተመራማሪዎች በአካባቢያቸው የሚገኙ ተግዳሮቶችን አልፎ ለመሄድ ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎች ላይ በማተኮር መስራት አለባቸው ብለዋል።

በትምህርት ቤቶች አሁን ላይ የሚታዩ የፈጠራ ስራዎች መነሳሳትን በማድነቅ የተማሪዎች የመፍጠር አቅም ማሳደግ ላይ የተጠናከረ ስራ ሊሰራ እንደሚገባ አመልክተዋል።

ተመራማሪዎች የሚያጋጥሟቸውን የቁሳቁስና የፋይናንስ ችግር ለመፍታት መንግስት ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በአለም አቀፍ ደረጃ በፈጠራው መስክ ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገቡ ኢትዮጵያውያን ምሁራን እንዳሉ ጠቅሰው፣ ይህንን አቅም በሀገር ውስጥ ለማስፋት የክልሉ መንግስት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ በበኩላቸው፣ መድረኩ በትምህርት ዘርፍ የተከናወኑ የፈጠራ ስራዎችንና ጥናቶችን ለማስተዋወቅ የተዘጋጀ ነው ብለዋል።


ቢሮው በክልሉ የሚገኙ የሳይንስና የፈጠራ አቅሞችን በቅንጅት ለመምራት፣ ለመደገፍና ለማልማት ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በትምህርት ስርዓቱ ተወዳዳሪነትንና ችግር ፈቺ እውቀትን ማስፋፋት የዘርፉ ቁልፍ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው፣ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት፣ ሃሳብና ተግባር ለማበልጸግ በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል።

በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ከሚፈልግና በትምህርት ጥራት ላይ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ከሚያደርግ ማንኛውም አካል ጋር ተቀናጅቶ ለመስራት ቢሮው ዝግጁ መሆኑንም አክለዋል።

በአዊ ብሔረሰብ ዞን የዚገም 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ10ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው አስማማው ሀብቴ እንደገለጸው፤ በራሱ ሀሳብ፣ አቅምና ጥረት ባለሶስት እግር ባጃጅ በመስራት የፈጠራ ስራውን አቅርቧል።


ፈጠራውም በሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ምርቶችን በተግባር መስራት እንደሚቻል ትልቅ ማረጋገጫ መሆኑን ገልጾ እንደዚህ ዓይነት ሲምፖዚየም መዘጋጀቱ ተነሳሽነትን እንደሚፈጥር አመልክቷል።

ለሶስት ቀናት በሚቆየው አውደ ርዕይና ሲምፖዚየሙ ላይም የምርምር ስራዎች የሚቀርቡ ሲሆን በሚያቀርቡት የፈጠራ ስራ ተወዳድረው ለሚያሸንፉ ተማሪዎች ሽልማት እንደተዘጋጀም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ፋውንዴሽኑ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች ድጋፍ እያደረገ ነው

ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...

Jun 23, 2026

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026