የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የተማሪዎችን የፈጠራ ተነሳሽነትና አቅም በሞራልና በቁሳቁስ መደገፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነት ሊሆን ይገባል

Jun 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦የተማሪዎችን የፈጠራ ተነሳሽነትና አቅም በሞራልና በቁሳቁስ መደገፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) ገለጹ።

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ክልላዊ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይና የጥናትና ምርምር ሲምፖዚየም በባህር ዳር ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።

በወቅቱም ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የተማሪዎችን የፈጠራ ተነሳሽነትና አቅም በሞራልና በቁሳቁስ መደገፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነት ሊሆን ይገባል።


ወጣት ተመራማሪዎች በአካባቢያቸው የሚገኙ ተግዳሮቶችን አልፎ ለመሄድ ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎች ላይ በማተኮር መስራት አለባቸው ብለዋል።

በትምህርት ቤቶች አሁን ላይ የሚታዩ የፈጠራ ስራዎች መነሳሳትን በማድነቅ የተማሪዎች የመፍጠር አቅም ማሳደግ ላይ የተጠናከረ ስራ ሊሰራ እንደሚገባ አመልክተዋል።

ተመራማሪዎች የሚያጋጥሟቸውን የቁሳቁስና የፋይናንስ ችግር ለመፍታት መንግስት ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በአለም አቀፍ ደረጃ በፈጠራው መስክ ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገቡ ኢትዮጵያውያን ምሁራን እንዳሉ ጠቅሰው፣ ይህንን አቅም በሀገር ውስጥ ለማስፋት የክልሉ መንግስት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ በበኩላቸው፣ መድረኩ በትምህርት ዘርፍ የተከናወኑ የፈጠራ ስራዎችንና ጥናቶችን ለማስተዋወቅ የተዘጋጀ ነው ብለዋል።


ቢሮው በክልሉ የሚገኙ የሳይንስና የፈጠራ አቅሞችን በቅንጅት ለመምራት፣ ለመደገፍና ለማልማት ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በትምህርት ስርዓቱ ተወዳዳሪነትንና ችግር ፈቺ እውቀትን ማስፋፋት የዘርፉ ቁልፍ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው፣ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት፣ ሃሳብና ተግባር ለማበልጸግ በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል።

በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ከሚፈልግና በትምህርት ጥራት ላይ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ከሚያደርግ ማንኛውም አካል ጋር ተቀናጅቶ ለመስራት ቢሮው ዝግጁ መሆኑንም አክለዋል።

በአዊ ብሔረሰብ ዞን የዚገም 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ10ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው አስማማው ሀብቴ እንደገለጸው፤ በራሱ ሀሳብ፣ አቅምና ጥረት ባለሶስት እግር ባጃጅ በመስራት የፈጠራ ስራውን አቅርቧል።


ፈጠራውም በሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ምርቶችን በተግባር መስራት እንደሚቻል ትልቅ ማረጋገጫ መሆኑን ገልጾ እንደዚህ ዓይነት ሲምፖዚየም መዘጋጀቱ ተነሳሽነትን እንደሚፈጥር አመልክቷል።

ለሶስት ቀናት በሚቆየው አውደ ርዕይና ሲምፖዚየሙ ላይም የምርምር ስራዎች የሚቀርቡ ሲሆን በሚያቀርቡት የፈጠራ ስራ ተወዳድረው ለሚያሸንፉ ተማሪዎች ሽልማት እንደተዘጋጀም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026