🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ በምግብ ራስን የመቻል ግብን ለማሳካትና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚያስችል ፈጣን የምርታማነት ሽግግር ላይ እንደምትገኝ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስትቲዩት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማንደፍሮ ንጉሴ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት “ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር” በሚል መሪ ሀሳብ የ“ኢትዮጵያ ታከናውናለች” ጉባኤ በሳይንስ ሙዚየም ተካሂዷል።

የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማንደፍሮ ንጉሴ (ዶ/ር) በጉባኤው ላይ የግብርና ዘርፍ የለውጥ ጉዞን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም ኢትዮጵያ በዘርፉ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ፣ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ጉልህ ማሻሻያዎችን ማከናወኗን ጠቅሰዋል።
በዚህም የሀገሪቱን የግብርና ዘርፍ ከነበረበት ከእጅ ወደ አፍ ልምምድ በማላቀቅ አሁን ላይ ከእርሻ ወደ ንግድ እና የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ወደሚያስችል ጠንካራ መሠረት እየተሸጋገረ ነው ብለዋል።
ለዚህም ከ10 ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣሙ ስትራቴጂዎችንና የፖሊሲ ማዕቀፎችን በመንደፍ፤ የመንግሥት፣ የግል ዘርፉንና የህዝብ አጋርነትን ለማጠናከር፣ ፈጠራንና የግብርና ቢዝነስን ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የግብርናው ዘርፍ ይበልጥ ምርታማ፣ በገበያ መር እና ለተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ተፅዕኖዎች የማይበገር የምርታማነት ሥርዓት እየተገነባ መሆኑን ገልጸዋል።
ቀደም ሲል ከውጪ በሚገቡ ምርቶች ላይ ጥገኛ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን ላይ በሀገር ውስጥ ተኪ ምርቶችን በማስፋት ተጨባጭ ውጤቶች በማምጣት ታሪኳን እየቀየረች ነው ብለዋል።
በስንዴ ምርት ራሷን ከመቻል አልፋ በአፍሪካ ቀዳሚዋ አምራች ሀገር መሆኗንም ተናግረዋል።
የሌማት ትሩፋትና መሰል በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎችን ያሳተፉ ሀገር በቀል ተነሳሽነቶችን በማዳበር፣ ቴክኖሎጂንና የሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም የግብርና ምርታማነት እያደገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በግብርናው ዘርፍ የተወሰዱ ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች ለዘላቂ የግብርና ልማት፣ ለገጠር ብልጽግና እና ለጠንካራ ኢኮኖሚ መሰረት መጣላቸውን ገልጸዋል።
ይህም ኢትዮጵያ ወደፊት እየተራመደችና ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበች መሆኑን በተግባር እንደሚያሳይ አመልክተዋል።
የግብርናው ዘርፍ ማሻሻያ የዘርፉን አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ድርሻ ማሳደጉን ተናግረዋል።
ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...
Jun 23, 2026
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026