የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ለቡና ልማት በተሰጠው ትኩረት የተመዘገበው ስኬት በዘርፉ ለተሰማሩ አርሶ አደሮች ትልቅ መነሳሳትን ፈጥሯል

Jul 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦መንግስት ለቡና ልማት በሰጠው ትኩረት የተመዘገበው ስኬት የኢክስፖርት ገቢን ከማሳደግ ባለፈ በዘርፉ ለተሰማሩ አርሶ አደሮች ትልቅ መነሳሳትን መፍጠሩን በባሌ ዞን የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው፣ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ ለቡና ልማት የተሰጠው ከፍተኛ ትኩረት ኢትዮጵያን በዓለም ሦስተኛዋ ቡና ላኪ ሀገር እንድትሆን ማስቻሉን ገልጸዋል።

አክለውም ሀገራዊ የሪፎርም ሥራው ለውጭ ምንዛሬ ግኝት ስኬቶች ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።

በዚህም በዘንድሮው ዓመት ኢትዮጵያ ከሸቀጦች ኤክስፖርት ያገኘችው ገቢ ከ11 ቢሊዮን ዶላር በላይ መሆኑን ገልጸው፣ ከቡና ኤክስፖርት ብቻ በዓመቱ 3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ የኮፊ አራቢካ መገኛ እንደመሆኗ መጠን በየትኛውም ዘመን ቡና ወደ ውጭ ስትልክ መቆየቷን ያወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ከለውጡ ዓመታት በፊት ግን ይህ ነው የሚባል ገቢ ማግኘት እንዳልተቻለ አስታውሰዋል።

በዚህም ሀገሪቱ ባለፉት 17 ዓመታት ቡናን ወደ ውጭ በመላክ በአጠቃላይ ያገኘችው ገቢ 3 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ብቻ እንደነበር ገልጸው፤ መንግሥት ለቡና ልማት በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት ግን በዘንድሮው ዓመት ብቻ 3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢን ማሳካት መቻሉን አነጻጽረው አብራርተዋል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የባሌ ዞን የግብርና ጽሕፈት ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች እንዳሉት፤ መንግሥት ለቡና ልማት በሰጠው ትኩረት የተመዘገበው ስኬት በዘርፉ ለተሰማሩ አርሶና አርብቶ አደሮች ትልቅ መነሳሳትን ፈጥሯል።


አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሙአዊያ ፉአድ፤ በዞኑ ባለፉት ዓመታት ለቡና ልማት በተሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ መመዝገቡን በማሳያነት አንስተዋል።

በዞኑ ከለውጥ ዓመታት በፊት በቡና ልማት የተሸፈነው መሬት ከ40 ሺህ ሄክታር እንደማይበልጥ ጠቅሰው፣ ከለውጡ ወዲህ ግን ልማቱን ወደ 78 ሺህ ሄክታር ማሳደግ መቻሉን አመልክተዋል።

በተጨማሪም ከአንድ ሄክታር የሚገኘውን የቡና ምርታማነት ከአምስት ኩንታል ወደ 10 ነጥብ 1 ኩንታል ማሳደግ መቻሉም የዘርፉ ትልቅ ስኬት መሆኑን ተናግረዋል።

ይህ ውጤት ሊገኝ የቻለው አርሶ አደሩ ያረጁ የቡና ተክሎችን በመጎንደልና ነቅሎ በአዲስ ምርጥ ዝርያ በመተካቱ መሆኑንም ጠቁመዋል።


የቡና ልማትን ለማስፋፋት በተሰጠው ትኩረት በየዓመቱ የሚተከለውን የቡና ችግኝ ከ15 ሚሊዮን ወደ 42 ሚሊዮን ማሳደግ መቻሉን የገለጹት ደግሞ በጽሕፈት ቤቱ የቡና፣ አትክልትና ቅመማ ቅመም ልማት ቡድን መሪ አቶ ወንደሰን ነጋ ናቸው።

በዚህም የዞኑ ዓመታዊ የቡና ምርት ከ15 ሺህ ቶን ወደ 44 ሺህ ቶን ማድረስ መቻሉ በዘርፉ ከተመዘገቡ ስኬቶች መካከል ተጠቃሽ መሆኑን አመልክተዋል።

በቀጣይም የቡና ልማትን ይበልጥ ለማስፋፋትና በሄክታር የሚገኘውን ምርታማነት ከ21 ኩንታል በላይ ለማድረስ፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ ሥራን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ኢኒሼቲቭ ተቀርጾ ወደ ሥራ መገባቱን አክለዋል።

አስተያየት ሰጪዎቹ በማጠቃለያቸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ላይ ለቡና ልማት የተሰጠው ትኩረት ኢትዮጵያን በዓለም ሦስተኛዋ ቡና ላኪ ሀገር እንድትሆን ማስቻሉን መግለጻቸው ትልቅ እምርታ መሆኑንና በዘርፉ ለተሰማሩ አርሶ አደሮችም የበለጠ የሥራ መነሳሳትን እንደሚፈጥርም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026