የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የዳኝነት አገልግሎትን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

Jul 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ሐምሌ 13/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ጋዛሊ አባሲማል ገለጹ።


በ6ኛው የጨፌ ኦሮሚያ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቧል።

ሪፖርቱን ያቀረቡት የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት አቶ ጋዛሊ አባሲማል፤ በክልሉ ፍትሐዊና ተደራሽ የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ገልጸዋል።

በዚህም የፍርድ ቤቶች የማስፈጸም አቅም ከመጨመሩ ባሻገር መዝገቦች ሳይጓተቱ በተቀመጠላቸው ጊዜ ውስጥ ተመርምረው ውሳኔ እንዲያገኙ መደረጉን ለአብነት ጠቅሰዋል።

በተለይም የዳኝነት አገልግሎትን በቪዲዮ ኮንፈረንስ ማካሄድ ባለጉዳዮች ከሩቅ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ በመደረጉ የባለጉዳዮችን እንግልትና ወጪ ማስቀረት እንደተቻለ ገልጸዋል።


ዜጎች ካሉበት ሆነው የፍትሕ ሂደቱን እንዲከታተሉና ምስክር እንዲያሰሙ በተዘረጋው የቴክኖሎጂ ሥርዓት ከ181 ሺህ በላይ የክስ መዝገቦች ላይ ውሳኔ ማግኘታቸውንም ጠቅሰዋል።

ከዚህም ባለፈ የሐሰት ማስረጃዎች በተወሰነ መልኩ እየቀነሱ መምጣታቸውን ገልጸው፣ የሥነ-ምግባር ችግር ባለባቸው ዳኞች ላይም እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አስረድተዋል።

በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 318 የሕግ ጥሰትና የዳኝነት ሥነ-ምግባር ጉድለት በፈጸሙ አካላት ላይ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን ጨምሮ የተለያዩ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንቱ በበጀት ዓመቱ ከ500 ሺህ በላይ መዝገቦች ላይ ውሳኔ በመስጠት የዓመታዊ ዕቅዱን 97 በመቶ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል።

በሌላ በኩል፣ በክልሉ በሥራ ላይ የሚገኙ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች እየሰጡ ባሉት አገልግሎቶች በመደበኛ ፍርድ ቤቶች ላይ የነበረው ጫና ከመቀነሱ ባለፈ አለመግባባቶች በሀገር በቀል እሴት መፍትሔ እንዲያገኙ ሆኗል ብለዋል።

በተመሳሳይ ሴቶች፣ ሕፃናትና አቅመ ደካሞች ነፃ የሕግ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ረገድ ውጤታማ ሥራዎች ተከናውነዋል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026