የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የዳኝነት አገልግሎትን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

Jul 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ሐምሌ 13/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ጋዛሊ አባሲማል ገለጹ።


በ6ኛው የጨፌ ኦሮሚያ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቧል።

ሪፖርቱን ያቀረቡት የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት አቶ ጋዛሊ አባሲማል፤ በክልሉ ፍትሐዊና ተደራሽ የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ገልጸዋል።

በዚህም የፍርድ ቤቶች የማስፈጸም አቅም ከመጨመሩ ባሻገር መዝገቦች ሳይጓተቱ በተቀመጠላቸው ጊዜ ውስጥ ተመርምረው ውሳኔ እንዲያገኙ መደረጉን ለአብነት ጠቅሰዋል።

በተለይም የዳኝነት አገልግሎትን በቪዲዮ ኮንፈረንስ ማካሄድ ባለጉዳዮች ከሩቅ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ በመደረጉ የባለጉዳዮችን እንግልትና ወጪ ማስቀረት እንደተቻለ ገልጸዋል።


ዜጎች ካሉበት ሆነው የፍትሕ ሂደቱን እንዲከታተሉና ምስክር እንዲያሰሙ በተዘረጋው የቴክኖሎጂ ሥርዓት ከ181 ሺህ በላይ የክስ መዝገቦች ላይ ውሳኔ ማግኘታቸውንም ጠቅሰዋል።

ከዚህም ባለፈ የሐሰት ማስረጃዎች በተወሰነ መልኩ እየቀነሱ መምጣታቸውን ገልጸው፣ የሥነ-ምግባር ችግር ባለባቸው ዳኞች ላይም እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አስረድተዋል።

በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 318 የሕግ ጥሰትና የዳኝነት ሥነ-ምግባር ጉድለት በፈጸሙ አካላት ላይ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን ጨምሮ የተለያዩ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንቱ በበጀት ዓመቱ ከ500 ሺህ በላይ መዝገቦች ላይ ውሳኔ በመስጠት የዓመታዊ ዕቅዱን 97 በመቶ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል።

በሌላ በኩል፣ በክልሉ በሥራ ላይ የሚገኙ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች እየሰጡ ባሉት አገልግሎቶች በመደበኛ ፍርድ ቤቶች ላይ የነበረው ጫና ከመቀነሱ ባለፈ አለመግባባቶች በሀገር በቀል እሴት መፍትሔ እንዲያገኙ ሆኗል ብለዋል።

በተመሳሳይ ሴቶች፣ ሕፃናትና አቅመ ደካሞች ነፃ የሕግ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ረገድ ውጤታማ ሥራዎች ተከናውነዋል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 17, 2026

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 11, 2026

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026