የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በዞኑ ከሁለት ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአትክልት እና ፍራፍሬ ተሸፍኗል

Jul 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነቀምቴ፣ሐምሌ 11/2018 (ኢዜአ)፡-በምስራቅ ወለጋ ዞን ከ ሁለት ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአትክልት እና ፍራፍሬ መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት አስታወቀ።

የምስራቅ ወለጋ ዞን የአትክልት እና ፍራፍሬ ባለሙያ አቶ ታከለ መኮንን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ በአትክልት እና ፍራፍሬ ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ እየተመዘገበ ነው።

በተለይ በአቮካዶ፣ ሙዝ፣ ማንጎ ፣ እና ፓፓያ ምርት ላይ ትኩረት ተደርጎ በመሰራቱ ውጤት ያስገኘ በመሆኑ አርሶ አደሩን ይበልጥ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል።

ለአብነትም በ2018 የምርት ዘመን 1 ነጥብ 7 ሚሊየን ኩንታል በላይ የተለያዩ ፍራፍሬዎችን ለማምረት ታቅዶ ከእቅድ በላይ 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ተችሏል ነው ያሉት ።

በዘንድሮው አመት በክላስተር እና በመደበኛ ከሁለት ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በላይ በፍራፍሬ እና አትክልት መሸፈን መቻሉን ገልጸዋል።

በዞኑ በፍራፍሬ እና በአትክልት ልማቱ ስራ ላይም 580 ሺህ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ መሆናቸውንም ገልፀዋል።

የምስራቅ ወለጋ ዞን ጉቶ ጊዳ ወረዳ አርሶ አደር ገለታ ውሉ ፤ላለፉት ሶስት አመታት በአቮካዶ ምርት ላይ በመሳተፍና የባለሙያዎችን መመሪያ ተግባራዊ በማድረግ ምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግ እንዳስቻላቸው ይገልፃሉ።

በሁለት ሔክታር መሬት ላይ በክላስተር አቮካዶን በማልማትም የተሻለ ምርት ለገበያ ለማቅረብ እየሰሩ መሆኑን ነው የሚገልጹት።

ሌላኛው አርሶ አደር አቶ ታሪኩ ነጋሳ በክላስተር የተለያዩ ፍራፍሬዎችን እያመረቱ እንደሚገኙ ገልፀው በዚህም ከራሳቸው አልፈው ለአካባቢው አምራች አርሶ አደር ልምድ እያካፈሉ መሆኑን ገልጸዋል።


ምርቱም ከምግብ በዘለለ በገቢ ምንጭነት እየተጠቀሙበት መሆኑን ነው የሚገልጹት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 17, 2026

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 11, 2026

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026