የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በከተማዋ የሚገነቡ መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ረገድ ውጤታማ የደንብ ማስከበር ስራ ተከናውኗል

Jul 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2018(ኢዜአ)፦ በከተማዋ የሚገነቡ መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ረገድ ውጤታማ የደንብ ማስከበር ስራ መከናወኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገለጹ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የስራ አፈጻጸም ግምገማ በማካሄድ ላይ ይገኛል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ፤ አዲስ አበባ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገች እና እየተለወጠች በመምጣቷ ለነዋሪዎቿ ምቹ መሆኗን ገልጸዋል።

ባለስልጣኑ የመሰረተ ልማቶችን የመጠበቅ፣ የመሬት ወረራን የመከላከል፣ ህገ-ወጥ ግንባታን የመከታተል፣ የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓቶችን የመቆጣጠር፣ ህገ-ወጥ ንግድን የመከላከል እና ሌሎች ተጨማሪ ተልዕኮዎችን ወስዶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ በከተማዋ የሚገነቡ መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ረገድ ውጤታማ የደንብ ማስከበር ስራ መከናወኑን ጠቁመው፣ ከሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀትም ከተማዋ ውብ እና ጽዱ እንድትሆን ያስቻሉ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወናቸውን ተናግረዋል።

የመሬት ወረራን በመከላከል እና ህገ-ወጥ ግንባታዎችን በመቆጣጠር ረገድ ስኬታማ ስራ መከናወኑን ጠቁመው፣ ህገ-ወጥ ንግድን በመከላከል ረገድ በተከናወኑ ስራዎችም የከተማዋ ጎዳናዎች ከህገ-ወጥ ንግድ ነጻ መደረጋቸውን አመልክተዋል።

ባለስልጣኑ ዲጂታል የቴክኖሎጂ ስርዓቶችን በመጠቀም የቁጥጥር ስርዓቱን ውጤታማ ማድረግ መቻሉን ጠቁመው፣ የደንብ ጥሰቶች ይፈጸሙባቸዋል ተብለው በሚታሰቡ አካባቢዎች ካሜራዎችን በመግጠም ከሲቹዌሽን ሩም በመሆን የዕለት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ግንባታ ፈቃድ እና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ህይወት ሳሙኤል የከተማዋን ስታንዳርድ ከማስጠበቅ ረገድ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በዚህም በከተማዋ ወጥ የሆነ የቀለም ስታንዳርድ መውጣቱን ተናግረው፣ በግንባታ ፈቃድ አሰጣጥ ዙሪያም በየአመቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ አልሚዎች በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመሩ መምጣታቸውን ገልጸዋል።

ባለፉት አምስት አመታት አዲስ አበባ በመዋቅራዊ ፕላኗ ብቻ እንድትመራ መደረጉን ጠቁመው፣ ህገ-ወጥ ግንባታዎች እንዲቀሩ በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል፡፡

የማስታወቂያ ቦርዶችን ዲጂታል ለማድረግ የተከናወኑ ስራዎች ለከተማዋ ተጨማሪ ውበት መፍጠራቸውን ገልጸዋል።

በቀጣዮቹ ጊዜያትም የህብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ እና ልማቱን ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 17, 2026

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 11, 2026

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026