የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የተፈጥሮ ማዳበሪያን በመጠቀማችን ወጪን ከመቀነስ ባለፈ ምርታማነታችን እያሳደገልን ነው - አርሶ አደሮች

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መቱ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በኢሉባቦር ዞን በቀያቸው አዘጋጅተው እየተጠቀሙ ያሉት የተፈጥሮ ማዳበሪያ ወጪ ከመቀነስ ባለፈ ምርታማነታቸውን እያሳደገ መሆኑን የዞኑ አርሶ አደሮች ገለጹ።


በኢሉአባቦር ዞን በበቾ ወረዳ የተፈጥሮ ማዳበሪያን በማምረት እየተጠቀሙ ካሉት አርሶ አደሮች መካከል ወይዘሮ አይናለም ጌታቸው አንዷ ናቸው።

ወይዘሮ አይናለም እንዳሉት፣ በግብርና ባለሙያዎች እገዛ ከአካባቢያቸው በሚገኙ ተረፈ ምርቶችና ዕፅዋት የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት መጠቀማቸው ከዚህ በፊት ለዘመናዊ ማዳበሪያ ይወጣ የነበረውን ወጪ ከማስቀረቱ በላይ የምርት መጠንን ማሳደጉን ገልጸዋል።


የዲዱ ወረዳ አርሶ አደሩ ገዳሙ አርፋሳ የተፈጥሮ ማዳበሪያን በማዘጋጀት ለእርሻ ሥራቸው እየተጠቀሙ መሆኑንና ከራሳቸው ፍጆታ አልፈው ለሌሎች በመሸጥ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ እንደሆናቸው ተናግረዋል።

የተፈጥሮ ማዳበሪያው የመሬት ለምነትን ጠብቆ የሚያቆይ በመሆኑ፣ ምርታማነት ለዓመታት ቀጣይነት እንዲኖረው ያስችላል ብለዋል።


በበቾ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ተስፋዬ ዲቤሳ እንደተናገሩት በወረዳው የምርትና ምርታማነት ዕድገትን ለማረጋገጥ አርሶ አደሮቹን ተጠቃሚ ለማድረግ በተፈጥሮ ማዳበሪያ ዙሪያ በተሠራው ሥራ ውጤት እየመጣ ነው።


የኢሉአባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ዳኜ ፍቅሬ እንደገለጹት በዞኑ በምርት ዘመኑ ከ265 ሺህ ኩንታል በላይ ዘመናዊ ማዳበሪያና ከ11 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው።

በዚህም የዞኑ አርሶ አደር ባለው መሬት ላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ አዘጋጅቶ በመጠቀም ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን አንስተው፣ ልምድም እያዳበሩ ነው ብለዋል።

በወረዳዎቹ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጃ ማዕከላት ተገንብተው ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቁመው ለአርሶ አደሮች እንዲደርስ መደረጉን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026