የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በምዕራብ ሸዋ ዞን ጤፍን በኩታ ገጠም በማልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ተችሏል

Jul 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ)፦በምዕራብ ሸዋ ዞን ጤፍን በኩታገጠም በማልማት የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ማሳደግ እንደተቻለ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዲዳ ጉደታ ገለፁ።

በዞኑ ኤጀርሳ ለፎ ወረዳ በመኸር አዝመራው በ4 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የጤፍ ሰብልን በኩታ ገጠም የመዝራት መርሃ ግብር ተካሂዷል።


የምዕራብ ሸዋ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዲዳ ጉደታ በመርሃ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት፤ በዞኑ በተያዘው የመኸር ወቅት ምርትና ምርታማነትን በመጨመር በምግብ ራስን ለመቻል የተጣለውን ግብ ለማሳካት እየተሰራ ይገኛል።

ከለውጡ ዓመታት ወዲህ ለግብርናው ዘርፍ በተሰጠው ከፍተኛ ትኩረትና የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በአግባቡ ለመጠቀም በመቻሉ ምርትና ምርታማነትን ለተከታታይ ጊዜያት ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል።


የምዕራብ ሸዋ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተረፈ አራርሳ በበኩለቸው እንዳሉት፤ በዞኑ የጤፍ ልማቱን በተሻለ መንገድ ስኬታማ ለማድረግና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየቱን እና በዚህም የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን አክለዋል።


በዞኑ በምርት ዘመኑ 84 ሺህ ሄክታር መሬት በጤፍ ዘር ለመሸፈን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አንስተው፣ እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴ 58 ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ገልፀዋል።

የኤጄርሳ ለፎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከበደ ለሊሳ በበኩላቸው ፤በተያዘው የመኸር ወቅት ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን በማቀድ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።


ከዚህ ውስጥም ከ12 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በጤፍ ሰብል ለማልማት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በዞኑ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እንዲቻልም የአፈር ማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር በተሻለ ሁኔታ መቅረቡን ጠቁመው አርሶ አደሩ የግብርና ፓኬጆችን ሙሉ በሙሉ እንዲተገብርም ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል።

በልማቱ እየተሳተፉ ካሉት የወረዳው አርሶ አደሮች መካከል አቶ ከበደ ፊጣ እና ዲዳ ጉታ፤ ባለፉት አራት ዓመታት ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር በመሆን በኩታ ገጠም ጤፍ በማልማት ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በአሁኑ ወቅትም ከወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት የምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን አግኝተው የእርሻ ስራዎችን በወቅቱ መጀመራቸውን ተናግረዋል።

በተያዘው የምርት ዘመንም ጠንክረውና ተቀናጅተው በመስራት ከአንድ ሄክታር እስከ 21 ኩንታል የጤፍ ምርት ለማግኘት አቅደው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 16, 2026

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 10, 2026

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 3, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 2, 2026