🔇Unmute
አምቦ፤ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ)፦በምዕራብ ሸዋ ዞን ጤፍን በኩታገጠም በማልማት የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ማሳደግ እንደተቻለ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዲዳ ጉደታ ገለፁ።
በዞኑ ኤጀርሳ ለፎ ወረዳ በመኸር አዝመራው በ4 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የጤፍ ሰብልን በኩታ ገጠም የመዝራት መርሃ ግብር ተካሂዷል።

የምዕራብ ሸዋ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዲዳ ጉደታ በመርሃ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት፤ በዞኑ በተያዘው የመኸር ወቅት ምርትና ምርታማነትን በመጨመር በምግብ ራስን ለመቻል የተጣለውን ግብ ለማሳካት እየተሰራ ይገኛል።
ከለውጡ ዓመታት ወዲህ ለግብርናው ዘርፍ በተሰጠው ከፍተኛ ትኩረትና የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በአግባቡ ለመጠቀም በመቻሉ ምርትና ምርታማነትን ለተከታታይ ጊዜያት ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል።

የምዕራብ ሸዋ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተረፈ አራርሳ በበኩለቸው እንዳሉት፤ በዞኑ የጤፍ ልማቱን በተሻለ መንገድ ስኬታማ ለማድረግና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየቱን እና በዚህም የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን አክለዋል።

በዞኑ በምርት ዘመኑ 84 ሺህ ሄክታር መሬት በጤፍ ዘር ለመሸፈን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አንስተው፣ እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴ 58 ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ገልፀዋል።
የኤጄርሳ ለፎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከበደ ለሊሳ በበኩላቸው ፤በተያዘው የመኸር ወቅት ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን በማቀድ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

ከዚህ ውስጥም ከ12 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በጤፍ ሰብል ለማልማት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እንዲቻልም የአፈር ማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር በተሻለ ሁኔታ መቅረቡን ጠቁመው አርሶ አደሩ የግብርና ፓኬጆችን ሙሉ በሙሉ እንዲተገብርም ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል።
በልማቱ እየተሳተፉ ካሉት የወረዳው አርሶ አደሮች መካከል አቶ ከበደ ፊጣ እና ዲዳ ጉታ፤ ባለፉት አራት ዓመታት ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር በመሆን በኩታ ገጠም ጤፍ በማልማት ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅትም ከወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት የምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን አግኝተው የእርሻ ስራዎችን በወቅቱ መጀመራቸውን ተናግረዋል።
በተያዘው የምርት ዘመንም ጠንክረውና ተቀናጅተው በመስራት ከአንድ ሄክታር እስከ 21 ኩንታል የጤፍ ምርት ለማግኘት አቅደው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026