የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ግልጽ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችሉ ዲጂታል መተግበሪያዎች ገቢራዊ ተደርገዋል

Jul 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018 (ኢዜአ)፦በነዳጅና ኢነርጂ ዘርፍ በዲጅታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ግልጽ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችሉ ዲጂታል መተግበሪያዎች ገቢራዊ መደረጋቸው የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን የነዳጅ ግብይቱን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥርዓት መቆጣጠር የሚያስችሉ መተግበሪያዎችን አስመርቋል፡፡


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ተቋማትን በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ በማደራጀት ምቹ የሥራ ከባቢና ቀልጣፋ አሠራር መዘርጋት ይገባል፡፡

ዘመኑን የዋጀ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሠራር ሥርዓት ለተቋማዊ ግንባታ የጎላ ሚና እንዳለው በመግለጽ፤ የዲጂታል አሠራር ቀጣይነት ይኖረዋል ብለዋል፡፡

የነዳጅና ኢነርጂ ዘርፉን አሠራር ይበልጥ ማዘመንና ግልጽነትን ማስፈን አስፈላጊ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ተመርቀው ሥራ ላይ የሚውሉት የዲጂታል ቴክኖሎጂዎች የላቀና ቀልጣፋ አገልግሎት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

ገቢራዊ የተደረጉት የዲጂታል መተግበሪያዎች የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አካል መሆናቸውን ገልጸው፤ ተቋማዊ አሠራርን በቴክኖሎጂ ማዘመን ቀጣይነት ይኖረዋል ብለዋል፡፡

የነዳጅ ዘርፉን ብልሹ አሠራር በሕጋዊ የአሠራር ሥርዓት ከመቆጣጠር ባሻገር በዲጂታል ቴክኖሎጂ መደገፍ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የተቀናጀ የነዳጅ ሥርዓት አበረታች ሥራ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ነገር ግን የበለጠ ግልጽነትን ለማስፈን ከ300 በላይ ዝርዝርና 47 ጥቅል አገልግሎቶችን በዲጂታል አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል ብለዋል፡፡

የመንግሥት መሻትና የሕዝብ ፍላጎት የሚሳካው አገልግሎቶችን ዘመኑን በዋጀ ቴክኖሎጂ መደገፍ ሲቻል መሆኑን በማንሳት፤ የዲጂታል መተግበሪያዎች የዚህ ማሳያዎች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡


የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ደስታው መኳንንት (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ባለሥልጣኑ ያለማቸው የዲጂታል መተግበሪያዎች ለተቋም ግንባታ መሠረት ይጥላሉ ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያን የአፍሪካ ብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ ለተጀመረው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግር ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የነዳጅ አቅርቦት ግብይትና ሥርጭት የተቋማትን አቅም መገንባት የሚያስችል መሆኑን ገልጸው፤ የዲጂታል መተግበሪያው በነዳጅ ዘርፍ 29 አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ፣ በኢነርጂ ዘርፍ 36 አገልግሎቶችን በከፊል በዲጂታል ቴክኖሎጂ መስጠት ተጀምሯል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026