የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ግልጽ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችሉ ዲጂታል መተግበሪያዎች ገቢራዊ ተደርገዋል

Jul 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018 (ኢዜአ)፦በነዳጅና ኢነርጂ ዘርፍ በዲጅታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ግልጽ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችሉ ዲጂታል መተግበሪያዎች ገቢራዊ መደረጋቸው የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን የነዳጅ ግብይቱን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥርዓት መቆጣጠር የሚያስችሉ መተግበሪያዎችን አስመርቋል፡፡


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ተቋማትን በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ በማደራጀት ምቹ የሥራ ከባቢና ቀልጣፋ አሠራር መዘርጋት ይገባል፡፡

ዘመኑን የዋጀ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሠራር ሥርዓት ለተቋማዊ ግንባታ የጎላ ሚና እንዳለው በመግለጽ፤ የዲጂታል አሠራር ቀጣይነት ይኖረዋል ብለዋል፡፡

የነዳጅና ኢነርጂ ዘርፉን አሠራር ይበልጥ ማዘመንና ግልጽነትን ማስፈን አስፈላጊ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ተመርቀው ሥራ ላይ የሚውሉት የዲጂታል ቴክኖሎጂዎች የላቀና ቀልጣፋ አገልግሎት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

ገቢራዊ የተደረጉት የዲጂታል መተግበሪያዎች የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አካል መሆናቸውን ገልጸው፤ ተቋማዊ አሠራርን በቴክኖሎጂ ማዘመን ቀጣይነት ይኖረዋል ብለዋል፡፡

የነዳጅ ዘርፉን ብልሹ አሠራር በሕጋዊ የአሠራር ሥርዓት ከመቆጣጠር ባሻገር በዲጂታል ቴክኖሎጂ መደገፍ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የተቀናጀ የነዳጅ ሥርዓት አበረታች ሥራ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ነገር ግን የበለጠ ግልጽነትን ለማስፈን ከ300 በላይ ዝርዝርና 47 ጥቅል አገልግሎቶችን በዲጂታል አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል ብለዋል፡፡

የመንግሥት መሻትና የሕዝብ ፍላጎት የሚሳካው አገልግሎቶችን ዘመኑን በዋጀ ቴክኖሎጂ መደገፍ ሲቻል መሆኑን በማንሳት፤ የዲጂታል መተግበሪያዎች የዚህ ማሳያዎች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡


የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ደስታው መኳንንት (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ባለሥልጣኑ ያለማቸው የዲጂታል መተግበሪያዎች ለተቋም ግንባታ መሠረት ይጥላሉ ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያን የአፍሪካ ብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ ለተጀመረው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግር ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የነዳጅ አቅርቦት ግብይትና ሥርጭት የተቋማትን አቅም መገንባት የሚያስችል መሆኑን ገልጸው፤ የዲጂታል መተግበሪያው በነዳጅ ዘርፍ 29 አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ፣ በኢነርጂ ዘርፍ 36 አገልግሎቶችን በከፊል በዲጂታል ቴክኖሎጂ መስጠት ተጀምሯል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉራጌ ዞን በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም  ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...

Jul 29, 2026

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...

Jul 29, 2026

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 16, 2026

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 10, 2026