🔇Unmute
ታርጫ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት 45 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በጀት አጸደቀ።
የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤውን በታርጫ ከተማ እያካሄደ ነው።
የክልሉ ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የኋላሸት በላይነህ፤ የክልሉ መንግስት የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 45 ቢሊዮን 700 ሚሊዮን 231 ሺህ 974 ብር መሆኑን ለጉባኤው በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

በጀቱ ከክልሉ ከሚሰበሰብ ገቢና ከፌደራል መንግስት ድጋፍ የሚሸፈን መሆኑን ተናግረዋል ።
የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ በበኩላቸው፤ በጀቱ በድህነት ቀናሽ ዘርፎች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ማህበራዊ አገልግሎትን ለማጠናከር ፣ ለስራ ዕድል ፈጠራ ፣ የኢንዱስትሪና የኤክስፖርት ምርቶች እንዲሁም መስኖ ልማት ጨምሮ ግብርና ስራዎችን ለማስፋትና ለፕሮጀክቶች ማጠናቀቂያ የሚውል መሆኑን አመላክተዋል።
ምክር ቤቱ በቀረበው የክልሉ የ2019 ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026