🔇Unmute
ታርጫ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት 45 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በጀት አጸደቀ።
የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤውን በታርጫ ከተማ እያካሄደ ነው።
የክልሉ ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የኋላሸት በላይነህ፤ የክልሉ መንግስት የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 45 ቢሊዮን 700 ሚሊዮን 231 ሺህ 974 ብር መሆኑን ለጉባኤው በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

በጀቱ ከክልሉ ከሚሰበሰብ ገቢና ከፌደራል መንግስት ድጋፍ የሚሸፈን መሆኑን ተናግረዋል ።
የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ በበኩላቸው፤ በጀቱ በድህነት ቀናሽ ዘርፎች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ማህበራዊ አገልግሎትን ለማጠናከር ፣ ለስራ ዕድል ፈጠራ ፣ የኢንዱስትሪና የኤክስፖርት ምርቶች እንዲሁም መስኖ ልማት ጨምሮ ግብርና ስራዎችን ለማስፋትና ለፕሮጀክቶች ማጠናቀቂያ የሚውል መሆኑን አመላክተዋል።
ምክር ቤቱ በቀረበው የክልሉ የ2019 ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...
Jul 29, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...
Jul 29, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...
Jul 16, 2026
መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...
Jul 10, 2026