🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦ ወጣቶች ክህሎታቸውን በማሳደግ ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስኬት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ከፍተኛ አማካሪ አብዮት ባዩ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቀረበውን የኢትዮጵያ ወጣቶች የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭን እንዲቀላቀሉ እና የክረምቱ ወቅት ከመጠናቀቁ በፊት የተሳታፊዎችን ቁጥር ወደ 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተደረገውን ሀገራዊ ጥሪ ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስተናጋጅነት በኢኒሼቲቩ ዙሪያ የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በመቀጠል በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ልምዳቸውንና እይታቸውን ያካፈሉ አራት ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ከፍተኛ አማካሪ አብዮት ባዩ (ዶ/ር) በፓናል ውይይቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፦ የላቁ የዲጂታል መድረኮችን መገንባት እና ሙሉ ለሙሉ ወደ ዲጂታል አሰራር መሸጋገር ግድ መሆኑን ገልጸው ለተግባራዊነቱና የዘመነ አፈጻጸም የሰለጠነ የሰው ኃይል እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።
የሰዎችን አቅም ማጎልበት፣ አሳታፊ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር፣ ተዳራሽነትን ማስፋፋት እና ሀገሪቱን የዲጂታል ማዕከል ማድረግ ላይ ትኩረት ባደረገው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ግቦች ስር እያንዳንዱ በቴክኖሎጂ ዘርፍ የሚመዘገብ ስኬት ሙሉ በሙሉ በሰው ሃይል አቅም ላይ የተመሰረተ እንደሆነ አብራርተዋል።
ይህን አቅም ወደ ተግባር ለመቀየር ደግሞ ወጣቶች በየተሰማሩበት ዘርፍ ክህሎታቸውን በንቃት ማሳደግ እና ለላቀ ውጤታማነት መጠንከር እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ጊምቢ፣ ነሐሴ4/2018 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን እየተተገበረ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ም...
Aug 11, 2026
ሰመራ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦ በአፋር ክልል የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል ...
Aug 10, 2026
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...
Jul 29, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...
Jul 29, 2026