የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ስንዴን በኩታገጠም በማልማታችን ምርታማነታችንን እያሳደግን ነው

Aug 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሸገር፤ ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፡- በሸገር ከተማ የኩራ ጂዳ ክፍለ ከተማ አርሶ አደሮች በዘመናዊ መንገድና በኩታገጠም የስንዴ ልማት ምርታማነታቸው መጨመሩን ገለጹ።

በኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ራስን ለመቻልና ሀገራዊ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በተቀየሰው ስትራቴጂ መሠረት፣ በኦሮሚያ ክልልና በሸገር ከተማ አስተዳደር የስንዴ ልማትን በስፋት የማስፋፋት ሥራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል።

በተለይም በሸገር ከተማ ኩራ ጂዳ ክፍለ ከተማ የሚገኙ አርሶ አደሮች ቀደም ሲል ይጠቀሙበት የነበረውን ባህላዊና አነስተኛ ይዞታን መሠረት ያደረገ የአመራረት ዘዴ በመተው፣ አቅማቸውን አዋህደው በኩታገጠም በማልማት ላይ ይገኛሉ።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ አርሶ አደሮቹ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከግብርና ሙያተኞች ያገኙትን ግንዛቤና ድጋፍ በመጠቀም ስኬታማ ሥራ እየሠሩ ይገኛሉ።

ከአርሶ አደሮቹ መካከል ወጣት ደቡ ሱልጣን እንደተናገረው፤ ባለፉት ዓመታት የግብርና ሥራችን ያልዘመነና ከፍተኛ ድካም የነበረበት ነው ይላል።

በአሁኑ ወቅት ግን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የኩታገጠም ግብርና መካሄዱ ከፍተኛ ውጤት እያስገኘልን ነው ብሏል።

አርሶ አደር ቡርኩ ታደሰ በበኩላቸው፤ ለዚህ ዓመት የግብርና ሥራ የሚያስፈልጉ ግብአቶች በወቅቱ በመቅረባቸው፣ በበለጠ ተግተን በልማት ሥራችን ላይ ተሰማርተናል ብለዋል።

አርሶ አደሩ በአካባቢያችን በኩታ ገጠም በመደራጀትና ያሉንን አቅሞች በማቀናጀት በልማቱ መሰማራታችን ቀድሞ ከምናገኘው ምርት የበለጠ በማግኘት ተጠቃሚ ሆነናል ብለዋል።

ሌላኛው አርሶ አደር ወጣት ተስፋዬ በቀለ አክሎ እንደገለጸው፤ የኩታ ገጠም ልማት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን ጠቁሞ፣ ይህም አርሶ አደሩ ሕይወቱን ከመቀየር ባሻገር ምርቱን ለገበያ በማቅረብ ለከተማዋ ኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው ነው ብሏል።

በልማቱ ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች አስፈላጊው ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑና የግብርና ግብአቶችንም በወቅቱ ማግኘታቸው ለሥራቸው ትልቅ መነሳሳት እንደሆናቸው ተናግረዋል።

በሸገር ከተማ የስንዴ ልማትን ማጠናከር የአርሶ አደሮችን ሕይወት ከመቀየር ጎን ለጎን፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የከተማዋን ኢኮኖሚ እድገት ለማፋጠን ከፍተኛ ሚና ያለው መሆኑን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማዋ የግብርና እና ልማት ክላስተር አስተባባሪ አቶ ግርማ ሀይሉ መግለጻቸው ይታወሳል።

በከተማዋ ኩራ ጂዳ ክፍለ ከተማ በ340 ሄክታር መሬት ላይ በኩታገጠም አሰራር ለምርጥ የስንዴ ዘር ብዜት የሚሆን የዘር መዝራት ስራ ትናንት ተከናውኗል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን እያሳደገልን ነው

ጊምቢ፣ ነሐሴ4/2018 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን እየተተገበረ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ም...

Aug 11, 2026

በአፋር ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ 

ሰመራ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦ በአፋር ክልል የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል ...

Aug 10, 2026

በጉራጌ ዞን በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም  ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...

Jul 29, 2026

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...

Jul 29, 2026