የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው

Aug 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ ከፍተኛ ርብርብ ሲደረግ መቆየቱንየከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ፡፡

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ለ19 ሺህ 698 የከተማዋ ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ የሚያደርግ ቦታ ለመስጠት የእጣ ማውጣት ስነ ስርአት አካሂዷል።


የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው በስነ ስርአቱ ላይ ባስተላለፉት መልእክት ዜጎችን የመኖሪያ የቤት ባለቤት የማድረግ ጉዳይ ከመንግስት የሰው ተኮር ፕሮጀክት አንዱ ነው።


የባህር ዳር ከተማን እድገት ለማፋጠን ከሚከናወነው የመሠረተ-ልማት ግንባታ ጎን ለጎን የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ ከፍተኛ ርብርብ ሲደረግ መቆየቱን ተናግረዋል።

በዛሬው ዕለትም በመንግሥት የትኩረት አቅጣጫ መሠረት በ901 ማህበራት ለተደራጁ 19 ሺህ 698 ዜጎች የብሎክ ዕጣ ማውጣት መቻሉን አስታውቀዋል።

የብሎክ ዕጣ ማውጣት የተቻለው የከተማ አስተዳደሩ ለቤት መስሪያ የሚሆን ቦታ አስፈላጊውን ካሳ በመክፈልና ከሦስተኛ ወገን ነፃ በማድረጉ መሆኑንም አመልክተዋል።

ከዚህ ቀደም እስከ 10 ዓመት ድረስ ይቆይ የነበረውን የቤት መስሪያ ቦታ የማቅረብ ሂደት አሁን ላይ በቴክኖሎጂ በመታገዝ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ማቅረብ የሚያስችል አቅም መፈጠሩን ገልጸዋል።

ይህም ዜጎች ተረጋግተው ተግባራቸውን እንዲከውኑ ለማድረግ ከማስቻሉም በላይ ከተማዋን ለኑሮ፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት የተመቸች ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።

የቤት መስሪያ ቦታው የሚሰጠው በወረብ፣ በአዲስ ዓለም፣ በመኮድና በሰልቸል ሳይቶች መሆኑንም አብራርተዋል።


የቦታው ተጠቃሚ የሚሆኑ ዜጎች ፈጥነው ወደ ግንባታ በመግባት ለወጣቶች የሥራ ዕድል፣ ለራሳቸውም ሀብት እንዲፈጥሩ አቶ ጎሹ አሳስበዋል።

በዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የከተማ አስተዳደሩ፣ የክልሉ ባለድርሻ አካላት እና የማህበራት ተጠቃሚ አባላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን እያሳደገልን ነው

ጊምቢ፣ ነሐሴ4/2018 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን እየተተገበረ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ም...

Aug 11, 2026

በአፋር ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ 

ሰመራ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦ በአፋር ክልል የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል ...

Aug 10, 2026

በጉራጌ ዞን በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም  ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...

Jul 29, 2026

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...

Jul 29, 2026