የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በምስራቅ ሐረርጌ  ዞን ቁንቢ ወረዳ  የተገነቡ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተመርቀው አገልግሎት መስጠት ጀመሩ

Aug 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቁንቢ፤ ነሐሴ 09/2018 (ኢዜአ) ፦በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ቁንቢ ወረዳ በ640 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነቡ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተመርቀው አገልግሎት መስጠት ጀመሩ።

በወረዳው ሀሮ ጉራቲ እና ሀሪሮ ቀበሌዎች የተገነቡትን ፕሮጀክቶች መርቀው ሥራ ያስጀመሩት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሡልጣን ወሊ (ዶ/ር) እና ሌሎች የክልሉና የምስራቅ ሐረርጌ ዞን አመራር አባላት ናቸው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኢነርጂ ዘርፍ ከሚተገበሩ የልማት ተግባራት መካከል የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም ሲሆን የኢትዮጵያ ኤልክትሪክና ብርሃን ተደራሽነት ፕሮጀክት ደግሞ በዚህ ፕሮግራም ስር ይከናወናል።

ከዋናው የብሔራዊ የኤሌክትሪክ መስመር ርቀው በሚገኙ እንደ ቁምቢ ወረዳ ሃሮ ጉራቲ እና ሃሪሮ ባሉ የገጠር ቀበሌዎች የሚዘረጉ የሶላር ሚኒ ግሪዶች ፣ ዘላቂና ንጹህ የሃይል አማራጭን ለህብረተሰቡ ለማቅረብ የተነደፉ ናቸው።

የምስራቅ ሐረርጌ ዞን፣ በተለይም ቁምቢ ወረዳ እና አካባቢው በቆላማና በከፊል አርብቶ አደር አየር ንብረት ክልል ውስጥ የሚገኙ በመሆናቸው በንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረትና ተደጋጋሚ የድርቅ ስጋት የሚታይባቸው አካባቢዎች ናቸው።

አሁን በእነዚህ ቀበሌዎች የተገነቡትን የውሃ እና የኢነርጂ ፕሮጀክቶች አጠናቆ ማስመረቅ ለአካባቢው ማህበረሰብ ዘላቂ ጥቅም የሚያስገኝ ትልቅ እርምጃ መሆኑ ነው የተገለጸው።

640 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው ፕሮጀክቶቹ 850 ኪሎ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላቸውና የ24 ሰዓት አገልግሎት መስጠት እንደሚችሉ በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ ተገልጿል።

ፕሮጀክቶቹ 3ሺህ 646 አባወራዎችን እንዲሁም የጤና፣ ትምህርትና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።

የወረዳው ነዋሪዎች በፕሮጀክቱ ግንባታ የዘመናት የልማት ጥያቄያቸው በመመለሱ ደስተኛ መሆናቸውን ነው የገለጹት።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የፌዴራልና የክልል፣ የዞንና ወረዳ አመራር አባላት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን እያሳደገልን ነው

ጊምቢ፣ ነሐሴ4/2018 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን እየተተገበረ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ም...

Aug 11, 2026

በአፋር ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ 

ሰመራ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦ በአፋር ክልል የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል ...

Aug 10, 2026

በጉራጌ ዞን በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም  ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...

Jul 29, 2026

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...

Jul 29, 2026