የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን እያሳደገ የሚገኘው ኮደርስ

Sep 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፦ የኮደርስ ስልጠና ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር ለመራመድና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገላቸው መሆኑን ስልጠናውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ገለፁ።

የ''አምስት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ’’ ስልጠና ሐምሌ 2016 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ መደረጉ ይታወሳል።

መርሃ ግብሩ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት 5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያንን በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዳታ ሳይንስና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት እንዲጨብጡ ለማስቻል ያለመ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተያዘው ክረምት ወቅት የ5 ሚሊየን የኮደርስ መርሐ ግብር ወደ 7 ሚሊየን ከፍ ለማድረግ ጥሪ ማቅረባቸውም ይታወሳል።

የኮደርስ ስልጠናን የተከታተሉ ሰልጣኞች ለኢዜአ እንዳሉት ስልጠናው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።

በኮተቤ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ የ11ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው ዕፁብ የወንድወሰን ስልጠናን በተመቸ ጊዜ መውሰድ የሚቻልና ከክፍያ ነፃ የሆነ ዕድል መሆኑን ተናግራለች።

ስልጠናው ከዘመኑ ጋር ለመራመድ የሚያስችል ራስን ማብቂያ መንገድ ነውም ብላለች።

በሳውዝ ዌስት አካዳሚ የ11ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ነቢዩ ዳዊት፣ ከትምህርት ሰዓቱ ጋር በማጣጣም በቀን ለ30 ደቂቃ ያህል ስልጠናውን በመከታተል ማጠናቀቁን ገልጿል።


ሌሎችም ወጣቶች የኮደርስን ስልጠናን በመውሰድ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን ማሳደግ እንዳለባቸው ጠቁሟል።

የአዲስ አበባ ከተማ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ቱሉ ጥላሁን (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት እንደ ሀገር የኮደሮችን ቁጥር ወደ 7 ሚሊየን ለማድረስ የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እየተሰራ ነው።

ቀደም ሲል በአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያን ኮደርስ እቅድ ለአዲስ አበባ የተመደበው 809 ሺህ ለማሰልጠን እንደነበርና ሀገራዊ እድቀዱ ወደ ሰባት ሚሊዮን ማደጉን ተከትሎ ወደ 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ከፍ ማለቱን አንስተዋል።


እስካሁን ባለው ለመመዝገብ ከታቀደው ውስጥ ወደ 985 ሺህ ዜጎች መመዝገባቸውንና ከእነዚህ ውስጥም 871 ሺህ ስልጠናቸውን አጠናቅቀው የምስክር ወረቀት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

ቢሮው የተለያዩ መድረኮችን በመጠቀም የግንዛቤ ስራዎችን በማከናወንና ከተቋማት ጋር በመቀናጀት ዕቅዱን ለማሳካት እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በቀሪ ጊዜያትም የተማሪዎች ላብራቶሪዎችን፣ የወጣቶች ማዕከላትን፣ ቤተ መጻሕፍትን እና የተለያዩ የማህበረሰብ መድረኮችን በመጠቀም ዕቅዱን ለማሳካት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026