የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ዘርፉን ለማሳለጥ ቅንጅታዊ አሰራሮችን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል- ምክትል ርእሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ./ር)

Sep 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር፤ ነሃሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ዘርፉን ለማሳለጥ የሚያስችሉ ዘመናዊ አሰራሮችን በመከተል ቅንጅታዊ አሰራሮችን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ./ር) ገለጹ።

የአማራ ክልል መንገድ፣ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ እያካሄደ ነው።


በመድረኩ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)፤ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አማራጮችን በማስፋትና በማሳለጥ ረገድ የተቀናጀ ጥረት ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በአገልግሎቱ የሚስተዋሉ ክፍተቶችንና ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን ለመከላከል ጥብቅ ቁጥጥርና ዘመናዊ የአሠራር ሥርዓትን መከተል እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የምርት እንቅስቃሴ በአግባቡ እንዲሳለጥና ኢኮኖሚው ላይ እመርታዊ አስተዋጽኦ እንዲኖረው ሥራዎችን ማከናወን ተገቢ መሆኑን አንስተው፣ ለዚህም ቅንጅታዊ ጥረቱ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

ለዚህም የክልሉ መንግሥት ለሦስቱም ዘርፎች በየዓመቱ ከፍተኛ በጀት በመመደብ በዘርፉ እመርታዊ ዕድገት ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።

በተለይ የመንገድ መሠረተ ልማትን በመገንባት ተደራሽነቱን ለማስፋት የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት የተመዘገበባቸው በመሆኑ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

በአዲሱ በጀት ዓመትም መልካም ተሞክሮዎችን በማስፋትና ክፍተቶችን ለይቶ በማረም የመንገድ መሠረተ ልማት ትስስሩን ለማሳለጥ በትኩረት እንደሚሠራ አስገንዝበዋል።

በትራንስፖርት ዘርፍም በአገልግሎት አሰጣጥ፣ ስምሪትና ሌሎች ተግባራት የሚስተዋለውን ውስንነት በመቅረፍ ሕዝቡ የተሳለጠ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲያገኝ ተሠርቷል ብለዋል።

በተጨማሪም የሎጂስቲክስ አቅምን በማሳደግ በክልሉ የሚመረተውን ምርት ከብክነት በጸዳና በጥራት አከማችቶና አጓጉዞ ለገበያ ለማቅረብ የተጀመረው ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

ዘርፎቹ በአዲሱ በጀት ዓመትም በውጤታማነት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በየደረጃው የሚገኘው አመራር ተቀናጅቶና ተባብሮ ሊሠራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የአማራ ክልል መንገድ፣ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ቢሮ ኃላፊ ጋሻው አወቀ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት አፈጻጸም የተሻለ ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን አብራርተዋል።

ከዚህ ስኬት በመነሳትም በተያዘው በጀት ዓመት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ የተሻለ እመርታ ለማስመዝገብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አንስተዋል።

የዚህ መድረክም ዋና ዓላማ የዘርፉን ስኬቶች ለማስቀጠል፣ ድክመቶችንና ጎደሎዎችን ለማስተካከል በሚያስችል መልኩ ለመገምገም መሆኑን ገልጸዋል።

ለሌሎች ሴክተሮችም የዕድገት መሠረት የሆነውን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ በትብብርና ቅንጅት መምራት አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

በቴክኖሎጂ የተደገፈ የትራንስፖርት አገልግሎት ለተገልጋዩ ሕብረተሰብ ለመስጠት የሚያስችል አቅም መፈጠሩ ለቀጣይ ሥራ መሠረት ነው ብለዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026

የአርብቶ አደሩን ማሕበረሰብ ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ስኬታማ ናቸው

ጂንካ፤ ነሐሴ 12/2018(ኢዜአ) ፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ አርብቶ አደሮችን ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን...

Aug 19, 2026