🔇Unmute
ጅግጅጋ፣ጳጉሜን 1/2018(ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት እውን እያደረጉ መሆኑን የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ አህመድ ረሺድ ገለጹ።
በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብትና ምቹ እድሎች በመጠቀም በሁሉም ዘርፎች የተቀናጀ የልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በዚህም ባለፉት ጥቂት ዓመታት ተጨባጭ ውጤትና ቀጣይነት ያለው ስኬት እየተመዘገበ ህዝቡም ተጠቃሚ መሆን ችሏል።
በክልሉ ጳጉሜን 1 "የእምርታ ቀን" እነዚህን ስኬቶች በማስታወስ ለቀጣይ የልማት ስራዎች ይበልጥ ለመትጋት በሚያስችል ሁኔታ እለቱ በጅግጅጋ ከተማ ተከብሯል።

በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የሶማሌ ክልል የኢንቨስትመንትና የኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ አህመድ ረሺድ፤ ከልማት እርቆና ተረስቶ የቆየው የሶማሌ ክልል ያልተቋረጠ ልማት ላይ ይገኛል ብለዋል።
በዚህም ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት እውን እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጠናቀቀው በጀት አመት ብቻ 530 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ መግባታቸውን ለአብነት አንስተው ከምርትም ባለፈ ለበርካታ ዜጎች ስራ መፍጠሩን ተናግረዋል።
የክልሉ የግብርና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አብዱረህማን ኑር በበኩላቸው በመደበኛ የምርት ወቅቶችና በመስኖ ጭምር በማልማት የክልሉ የግብርና ምርታማነት እያንሰራራ መምጣቱን ገልጸዋል።

በዚህም የምግብ ዋስትናንና የቤተሰብ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የራሱን ድርሻ ማበርከቱን አስረድተዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ የሥራ ሃላፊዎች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026