የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የዲጂታል ኢኮኖሚና መሰረተ ልማትን በማስፋት አንድነትንና ልማትን የሚያጠናክር ነገን እየገነባን ነው

Sep 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚና መሰረተ ልማት በማስፋት አንድነትና ልማትን የሚያጠናክር አውድ መፍጠር የሚያስችል ነገን እየገነባን ነው ሲሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከሌሎች የፌዴራል ተቋማት ጋር በመተባበር ነገ ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከብረውን የ"ነገ ቀን" በማስመልከት መግለጫ ሰጥቷል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መንግሥት የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ስያሜዎች እያከበረ ይገኛል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር በዲጂታል ኢኮኖሚ የዳበረች ኢትዮጵያን ለማስረከብ የሚከናወኑ ተግባራትን የሚያሳየው የነገ ቀን ይከበራል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን በመቅረጽ የዲጂታል ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ሥራ እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል።

በዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም የጎለበተ፣ ዘመኑን የዋጀ ሲቪል ሰርቪስ በመገንባት፣ ፈጣንና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት በመስጠት ምን ዓይነት ነገን እንገንባ በሚለው ላይ መሠረት እየጣልን ነው ብለዋል።

ነገ ማለት ወጣቶች የሚረከቧት ኢትዮጵያ ማለት ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ለትውልዱ የአንድነት፣ የሰላምና የልማት አውድ መፍጠር የሚያስችል ነገን ለመገንባት መሆኑን ገልጸዋል።

አዲስ ዓመት አዲስ ተስፋና ሀሳብ መፈጠሪያ መሆኑን ገልጸው፤ ለሕዝባችን የገባነውን ቃል በተግባር መፈጸም ይገባናል ብለዋል።

አዲሱ ዓመት ፈተናዎችን አልፈን የተሳካ ሰላምና ልማት የምናስመዘግብበት እንዲሆን እመኛለሁ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026