አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 4/2017(ኢዜአ)፦ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሥርዓትንና ሕግን አክብሮ መተግበር ከተቻለ የዜጎችን፣ የሀገርንና የተቋማትን ተወዳዳሪነት ማሳደግ ይቻላል ሲሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በቀረፀው የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ከውጭ ሀገር የሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡
በመድረኩ የተገኙት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሥርዓትንና ሕግን አክብሮ መተግበር ከተቻለ የዜጎችን፣ የሀገርንና የተቋማትን ተወዳዳሪነት ማሳደግ ይቻላል ብለዋል፡፡
ሚኒስቴሩ ሥነ-ምህዳሩን ምቹ በማድረግ ኤጀንሲዎች ሚናቸውን እንዲወጡ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ መግለጻቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡
በተጨማሪም ኢንዱስትሪውን ለመቀየር ብቁ የኤጀንሲዎች ስብስብ በማፍራት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በላቀ ትጋት እየሠራ እንደሚገኝም አብራርተዋል፡፡
ይሁን እንጂ በዘርፉ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ሚናቸውን በኃላፊነት ከመወጣት ይልቅ ሕጋዊ አሰራርን በማይከተሉ ኤጀንሲዎች ሳቢያ ዜጎችን ለእንግልትና ለስቃይ የሚዳርጉ አጋጣሚዎች በተደጋጋሚ መከሰታቸውን ጠቁመዋል፡፡
መሰል ሕገ-ወጥ ድርጊቶችን በመከላከል የዜጎችን ክብርና ደህንነት ማዕከል ያደረገ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ሥርዓት እውን ለማድረግ የአዋጅ ማሻሻያ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱንም ጠቁመዋል፡፡
ሕጋዊ አሠራርን ተከትለው ለዜጎች ተገቢውን አገልግሎት ለሚሰጡ ኤጀንሲዎች እውቅና መስጠት የሚያስችል አሠራር ለመዘርጋት ጥናት እየተካሄደ መሆኑን ሚኒስትሯ ገልጸዋል፡፡
አሁን በሥራ ላይ የሚገኙ ኤጀንሲዎችን በማሰባሰብ የተሻለ አቅም እንዲፈጥሩ የሚያግዝ ወጥ የሆነ አደረጃጀት በቀጣይ ለመፍጠር መታቀዱን መናገራቸውም በመረጃው ተመላክቷል፡፡
የውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት በፍጹም ሥነ ምግባር፣ በሃላፊነትና ሀገርን በመውደድ ስሜት ሊተገበር እንደሚገባም ነው ሚኒስትሯ ያሳሰቡት፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025