የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረኦ ሀሰን፤ የቻይና ኮሙኒኬሽንስ ኮንስትራክሽን ኩባንያ (CCCC) የገዛቸውን 92 ዘመናዊ የኤሌክትሪክ የጭነት ተሽከርካሪዎች በእንዶዴ ባቡር ጣቢያ በመገኘት ሥራ አስጀምረዋል፡፡


እነዚህ ተሽከርካሪዎች ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ በመሆናቸው፣ መንግሥት ከያዘው የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስትራቴጂ ጋር የተጣጣሙ መሆናቸው ተገልጿል።

ተሽከርካሪዎቹ ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ግንባታ አገልግሎት የሚውሉ መሆኑም በዚሁ ወቅት ተጠቁሟል፡፡

ሚኒስትር ዴኤታው በረኦ ሀሰን በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ መንግሥት የትራንስፖርት ዘርፉን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።

በተለይም በሀገሪቱ እየተገነቡ ባሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ የሚሰማሩ ተሽከርካሪዎችና መሣሪያዎች ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በስፋት ጥቅም ላይ እንዲውሉ በተዘረጋው አሠራር፣ በአሁኑ ወቅት 17 ድርጅቶች በሀገር ውስጥ የመገጣጠም ሥራ መጀመራቸውን አመልክተዋል።

እነዚህ ድርጅቶች ከሁለት እግር ተሽከርካሪዎች ጀምሮ እስከ 400 ኩንታል የመሸከም አቅም ያላቸውን የጭነት ተሽከርካሪዎች እየገጣጠሙ እንደሚገኙም አብራርተዋል።

በተጨማሪም የመንግሥት ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች የሚገዟቸው ተሽከርካሪዎች እንዲሁም የከተማ የሕዝብ ትራንስፖርት ባሶች ሙሉ በሙሉ የኤሌክትሪክ እንዲሆኑ መወሰኑን ጠቅሰዋል።

ዘርፉን ይበልጥ ለማበረታታትም ነዳጅ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ለመቀየር የሚያስፈልጉ የቴክኖሎጂ ግብዓቶች ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ መደረጉን አስታውሰዋል።

በዘርፉ የግሉን ተሳትፎ ይበልጥ ማሳደግ የሚያስችሉና የሚያበረታቱ አሰራሮች እየተዘረጉ መሆኑን ገልጸው፤ በዚህም ተጨባጭ ውጤቶች እየመጡ መሆኑን ተናግረዋል።

አሁን በቻይናው ተቋራጭ ተገዝተው የገቡት የሲኖ ብራንድ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ከፍተኛ ጥራት ያላቸውና ለሀገሪቱ የአረንጓዴ ልማት ጉዞ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚኖራቸው መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026